የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ከእስራኤል የቱሪዝም ሚንስትር ጋር ተወያዩ፤የእስራኤል ሙዝየምንም ጎበኙ።

December 13, 2023

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በቅድስት አገር ኢየሩሳሌም የሚያደርጉትን ሐዋርያዊ አገልግሎት ቀጥለዋል።
በቅድሚያ በቅድስት አገር ኢየሩሳሌም በደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን በመገኘት ጸሎተ ኪዳን አድርሰዋል ።

በመቀጠልም በታሪካዊ ይዘቱ በዓለም ላይ ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ሙዝየሞች መካከል አንዱ የሆነውን የእስራኤልን ሙዝየም ጎብኝተዋል። በሙዝየሙ ሲደርሱ ከእስራኤል መንግሥት የፕሮቶኮል አቀባባል ተደርጎላቸዋል። የሙዝየሙ ጉብኝት ዓላማ በክርስትናና በአይሁድ ሃይማኖቶች መካከል ያለውን ተዛምዶ በእውነት ላይ ተመስርቶ መረዳት ነው።

በጉብኝቱም የአባታችን አዳም ከድቀት በኋላ የነበረውን ገጽታ የሚያሳይ ምስለ ቅርጽ፣ ዕፀ በለሷ ከተበላች በኋላ የነበራት ምስል፣ እስራኤል ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር በተለይም ከክርስትና እምነት ጋር ያላት ታሪካዊ ግንኙነት፣ አክሱም ተቆፍረው ከተገኙት ሳንቲሞች (coins ) ተመሳሳይነት ያላቸው ሳንቲሞች፣ የኢየሱስ ክርስቶስመቃብር፣ እግሩ የተቸነከረበት ችንካርና በአፍሪካ ሙዝየም ውስጥ ጎልቶ የሚታየውን የኢትዮጵያ ክፍል (በክፍሉ ውስጥ ሁሉም በሚያሰኝ መልኩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሀብት የሆኑ የብራና መጻሕፍት ፣ ንዋያተ ማኅሌት፣ የካህናት መገልገያዎች ናቸው) ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ማጠቃለያ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ እንደገለጹት በትንሽ ሀብትና አነስተኛ እድሜ ያላቸውን ቅርሶች አሰባስቦ በዚህ መልክ ለዐይን በሚስብ ውብና ማራኪ በሆነ አቀራረብ ለህዝብ ዕይታ ማዘጋጀት ከተቻለ ረጅም እድሜና ሰፊ ታሪክ የሰው ልጅ የታሪክ ባለቤትነት የሚረጋገጥባት ኢትዮጵያና እራሷ ቅርስ ሆና ቅርሶችን እየጠበቀችና እየተንከባከበች የምትገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅርሶቿን በዚህ መልኩ አደራጅታ ለዓለም ብታቀርብ በምጣኔ ሀብትም ሆነ በቱሪዝም ፍሰት ወደር የማይገኝላት አገር ልትሆን ትችላለች።

ከዚህ ያየነውን ልምድ ቀምረን ለመጠቀም እንደ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በፈቃደ እግዚአብሔር ጥረት የምናደርግ ይሆናል ብለዋል። በተለይም የኢየሩሳሌም ሞዴል ከተማን በተመለከተ ኢትዮጵያውያንም የዛሬ ማንነታችን የቆመው በትላንታችን መሆኑን ተገንዝበን ታሪኮቻችን መገናኛ ድልድዮቻችን እንጅ ማለያያ የጥላቻ ግርዶሾቻችን እንዳይሆኑ እንደ እስራኤላውያን በትጋት መሥራትና ሁሉንም ሰንዶ አስተማሪ ማድረግ ይኖርብናል ። እየገጠመን ላለው መከራም መድኃኒቱ ታሪክን ለትውልድና ለሀገር ግንባታ ማዋል ነው በማለት አጸጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

በመጨረሻም ከእስራኤል መንግሥት ቱሪዝም ሚንስትር ከአቶ ሃም ካትስ ጋር ኢትዮጵያውያን ለልደት፣ ለትንሣኤ ና ለልዩ ልዩ በአላት ወደ ቅድስት አገር ኢየሩሳሌም ሊመጡ ሲያስቡ ያለምንም መንገላታት ቪዛ በሚያገኙትበት ሁኔታ ላይ ተወያይተዋል።

ክቡር ሚንስትሩም የቆየ ታሪካዊ ግንኙነትና የደም ትስስር ካለን ከኢትዮጵያ ጋር ሃይማኖታዊ ጉዞዎች ያለምንም እንከን እንዲካሄዱ ማድረግ ግዴታችን ነው። ለኢትዮጵያውያን ልዩ እንክብካቤ ለማድረግ እንጥራለን ብለዋል።

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅም ስለተደረገላቸው የክብር አቀባበል አመስግነው ለእስራኤልና በአካባቢው ላሉ አገራት እግዚአብሔር አምላክ ሰላም ፍቅር ስምምነት እንዲሰጣቸው ጸልየዋል።

ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ከጉብኝቱ በኋላ በባለ አምስት ኮከብ ሆቴል የተያዘላቸውን ፕሬዘንደንታዊ ክፍል በመተው ማረፊያቸውን በደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን አድርገዋል።

በጉብኝቱና በውይይቱ ወቅት ከብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ ጋር አብረው የተጓዙ የድል፣ የትንሣኤ፣የአዳ፣ የአፍሮ ሆሊ ላንድና ቆሮንቶስ አስጎብኝ ድርጅቶች ባለቤቶችና የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተዋል።©EOTC TV

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና ጊዜያዊ ርዳታም አበረከተ።
  • “በአርሲ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንሠራለን” የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች
  • ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በሀገረ ስብከቱ ለካህናት የሚሰጠውን ሥልጠና በጸሎትና በቡራኬ አስጀመሩ።
  • ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ተገኝተው የተጎዱ ወገኖችን የሚያጽናኑ በፁዐን አባቶችን መደበ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን የልዑካን ቡድን ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያየ።

Archives

  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: በወቅታዊ ጉዳዮች ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ Link to: በወቅታዊ ጉዳዮች ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ በወቅታዊ ጉዳዮች ከቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለ... Link to: ማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ባከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ከ7.5 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ Link to: ማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ባከናወነው የገቢ ማሰባሰቢያ መርሐ ግብር ከ7.5 ሚሊየን ብር በላይ መሰብሰቡን አስታወቀ፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን አዲስ አበባ ማእከል ባከናወነው...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top