የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ብፁዕ አቡነ በርተሎሜዎስ የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን አስመልክተው አባታዊ ቃለ በረከት አስተላለፉ።

January 7, 2025

ታኅሣሥ ፳፱ ቀን ፳፻ ፲፯ ዓ.ም

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

“የዲያብሎስን ሥራ እንዲያፈርስ የእግዚአብሔር ልጅ ተገለጠ።” ፩ኛ ዮሐ ፫÷፱

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት

ከሁሉ አስቀድሜ ልዑል እግዚአብሔር አምላካችን በሰላምና በጤና በሕይወት ጠብቆ አሁን ላለንበት ጊዜና ሰዓት ስላደረሰን ስሙ የተመሰገነ ይሁን።

ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ በጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ምን ያህል እንደከበርን ሲናገር
“በልደቱ ተወለድነ ወበጥምቀቱ ተጠመቅነ ወከብረ በዝንቱ ሕሱር ሥጋነ ” በመወለዱ ተወለድን በመጠመቁም ተጠመቅን በዚህም የተዋረደው ሥጋችን ከበረ ይላል።

ክብር ይግባውና ጌታችንና አምላካችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  ለአባታችን አዳም በገባው ቃል ካዳን መሠረት የሰው ልጅ ወደ ሚደነቅ ብርሃን ወጣ ጠላት ዲያብሎስ ላይፈታ ታሰረ ላይነሳ ወደ ሲኦል ረግረግ ተጣለ በስጋ ብዕሲ ተሰውሮ የሰውን ልጅ ድል የነሳውን ዲያብሎስን ክብር ይግባውና መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ “በከበረ በማርያም ማኅፀን ሥጋን ተዋሐድኩ” እንዳለ ሲራ ፳፬÷፲ እርሱም በሥጋ ብዕሲ በድንግል ማርያም ማኅፀን አድሮ ዲያብሎስን ድል አድርጎ የዘለዓለም ደስታና ረፍት ሰጠን

እንኳን ለ፳፻ ፲፯ ዓ.ም የጌታችንንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳቹ

ውድ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኦርቶዶክሳውያን በወርቅ ወይም በብር በከበረ ዕንቁ ያይደለ በከበረ ደሙ ፈሳሽነት የገዛን መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ለዚህ ታላቅ በዓል ስላደረሰን ስሙ የተመሰገነ ይሁን እኛ ሰው መሆን አቅቶን ባለንበት ዘመን በማይደበዝዝ ፍቅሩ ሰው ሆኖ በሥጋ ማርያም ተገልጦ ፍቅሩን ያሳየን የወደደን ፈጣሪ ስሙ የተመሰገነ ይሁን።

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ይባርክ!

አባ በርተሎሜዎስ
የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ታኅሣሥ  ፳፱ ቀን ፳፻ ፲፯ ዓ.ም
መረጃውን ያገኘነው ከሀገረ ስብከቱ ምዞብ ግንኙነት ነው።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና ጊዜያዊ ርዳታም አበረከተ።
  • “በአርሲ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንሠራለን” የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች
  • ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በሀገረ ስብከቱ ለካህናት የሚሰጠውን ሥልጠና በጸሎትና በቡራኬ አስጀመሩ።
  • ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ተገኝተው የተጎዱ ወገኖችን የሚያጽናኑ በፁዐን አባቶችን መደበ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን የልዑካን ቡድን ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያየ።

Archives

  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: መልእክተ ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል Link to: መልእክተ ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል መልእክተ ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል Link to: መልእክተ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ Link to: መልእክተ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ መልእክተ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ
Scroll to top Scroll to top Scroll to top