የካቲት ፩ ቀን ፳፻ ፲ወ፰ ዓ.ም

የአዲሱ ሕንፃ ቤተመቅደስ መሠረት ድንጋይ ሲቀመጥ የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም ዓለማየሁ ተፈራ ፣የወለቴ ደብረ ገሊላ ቅዱስ በዓለ ወልድና ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ዋና አስተዳዳሪ መልአከ ይባቤ ታደሰ ጌጡ ፣ የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኅላፊዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ፣ ካህናት አባቶች ፣ ዘማሪያን እንዲሁም ምእመናን ተገኝተዋል።

ብፁዕነታቸው የሕንፃ ቤተክርስቲያኑ መሰረት ድንጋይ መቀመጡን ተከትሎ ባስተላለፉት መልእክት ” እናንተ ከበረታችሁ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ሁኖ ይሠራል ፣ሥራውን የሚሰራ እግዚአብሔር ነው እናንተ አይደላችሁም ፤እግዚአብሔር በሰው ላይ አድሮ ነው ሥራ የሚሰራው ፣ስለዚህ ሁላችሀም ተባብራችሁ በአጭር ጊዜ መሥራት ነው”ብለዋል።

ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የአዲሱን ሕንፃ ቤተመቅደስ መሠረት ድንጋይ ባስቀመጡበት በዚሁ አገልግሎታቸው የደብሩን ፀበል ቤት ባርከው አገልግሎት ያስጀመሩ ሲሆን የጻድቁ አቡነ እጨጌ ዮሐንስ ታቦተ ሕግንም ወደ ቤተክርስቲያኑ አስገብተዋል።

ከዚህ በመለስ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገረ ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መሪነትና አዘጋጅነት በሸገር ከተማና ደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት በልዩ ልዩ አድባራት የሚከናወነው “ወጣትነት ለቤተክርስቲያን” የተሰኘው የትምህርተ ወንጌል አገልግሎትም ለ40ኛ ዙር በዚሁ ቤተክርስቲያን መከናወን ጀምሯል።

የወለቴ ደብረ ገሊላ ቅዱስ በዓለ ወልድና ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን በ2013 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የተመሰረተ መሆኑ ይታወቃል።