ለዘመናት የቤተክርስቲያንን ተልእኮ በማሳለጥ የሚታወቀው የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ በበጀት ዓመቱ ለሦስተኛ ጊዜ ዐቢይ ጉባኤ አካሄደ

ሚያዚያ ፲፱ ቀን ፳፻፲ወ፰ዓ.ም.
ኢኦተቤክ ሕዝብግንኙነት
አዲስአበባ ኢትዮጵያ
👉 እስከ ምድር ዳርቻ ምስክሮች ሊሆኑ ለተጠሩት ለቅዱሳን ሐዋርያት በመጀመሪያ የታወጀው አዋጅ የማይሻር፣ ለዘለዓለም ጸንቶ ከትውልድ ወደ ትውልድ እየተላለፈ ያለና ሲተላለፍ የሚኖር ሕያው ቃል በመሆኑ ብርሃናተ ዓለም ሐዋርያት፣ ሰባ ሁለቱ አርድዕት የስብከታቸውን ማዕከል ክርስቶስንና የአዳኝነቱን ሥራ በማድረግ አስዋከ ረሲዓንን እየነቀሉ፣ የወንጌልን ምርጥ ዘር በምዕመናን የልቡና ማሳ ላይ እየዘሩ በጋራም በተናጠልም ከፍተኛ ሐዋርያዊ ተጋድሎ የፈጸሙ ሲሆን ዘሩም በቅሎ አፍርቶ ፍሬው ከሐዋርያት ለሐዋርያነ አበው፣ ከሐዋርያነ አበው ለሊቃውንት ከሊቃውንት ወደ እኛ ዘመን መተላለፉ የሚታወቅ ነው፡፡
👉 የክርስቲያኖች ቁጥር እየጨመረ ሲመጣ በጥንድ እና በግል ሲመራ የነበረው የአመራር ስርዓት በመዋቅር የመምራት ስሌት ከመጣ በኋላም ብዙ አባቶቻችን ስለ ቤተክርስቲያን አያሌ ተግባራትን ማከናወናቸው ሌላኛው የስብከተ ወንጌል ፍሬ መሆኑም ይገለጻል።
👉 ለዘመናት በብዙ ፈተና ያለፈችው ቅድስት ቤተክርስታያናችን በ1950ዓ.ም ከግብፅ የአመራር
ስርዓት ወጥታ የራሷን ፓትርያርክ ከሾመች በኋላ በ1952ዓ.ም የመጀመሪያ ሥራዋን ያደረገችው የሀገሪቱን ንጉሥና ቅዱስ ፓትርያርኩ የበላይ ጠባቂነት የሚመራ ከሊቅ እስከ ደቂቅ ያሳተፈ የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ምክር ቤት ማቋቋም ሲሆን ምክር ቤቱ ከንጉሡ እና ከፓትርያርክ ጀምሮ ሁሉም ተስፋ የሚጥሉበት ስለነበረ ለአፈጻጸም የማይቸገር መሆኑን
ሊቃውንት ይገልጻሉ።
👉 የንጉሡ ዘመን ካለፈ በኋላም ሶሻሊዝምን አራማጁ የደርግ መንግሥት ለስብከተ ወንጌል ፈተና ቢሆንበትም ቅሉ ባለ ራዕዩ እና ልባሙ ቅዱስ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ አማካኝነት ሰበካ ጉባኤንና
ሰንበት ትምህርት ቤት ወልዶ ራሱን በመዋቅር በ1972ዓ.ም አዲስና ለእንቅስቃሴው በር ከፋች ስርዓት በመፍጠር ሲሰራ እንደነበረ የዓይን እማኞች ይናገራሉ።
👉 ከለውጡ ማግሥት በ1984 እና በ1988 ዓ.ም. ደግሞ በሌላኛው ፓትርያርክ ልዩ መተዳደሪያ ደንብ ተሠርቶለት ስብከተ ወንጌልን በማስፋፋቱ ረገድ አንቱ የተባለ ሥራ የተሠራ ሲሆን በ1992 ዓ.ም. ደግሞ ዓለም ዓቀፋዊ በሆኑት ፓትርያርክ በብፁዕ ወቅደስ አቡነ ጳውሎስ መመሪያ ሰጭነት በብፁዕ አቡነ ቄርሎስ የወቅቱ ሥራ አስኪያጅ አስፈፃሚነት የተቋቋመው የ120 ቤተሰብ የስብከተ ወንጌል ማስፋፊያ ኮሚቴ ደግሞ ሌላኛው የስብከተ ወንጌል ገፅታ ነው።
👉 በዚህ ልክ ራሱን እያሳደገ የመጣው የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ ዛሬም የምዕመናን ደጀንነቱንና የቤተክርስቲያን ብቸኛ ተስፋ መሆኑን በሚገልጽ መልኩ በየጊዜው ስልጠናዎችንና ውይይቶችን እየደረገ ነው።
👉 በዛሬው እለትም ይህንኑ ስልጠናና ውይይት በወንጌል ሕይወታች ሆነልን በሚል ርዕስ ያካሄደ ሲሆን በስልጠናው ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብጰት ሊቀ ጳጳስ፤
ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባ ፣ የሐድያና ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣
ክቡር ንቡረዕድ ኤልያስ አብርሃ የጠቅላይ ቤተክህነት የመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
ክቡር ረዳት ፕሮፌሰር ግርማ ባቱ የጠቅላይ ቤተክህነት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ፤
ክቡር ሊቀ ኅሩያን ይልማ ጌታሁን የኢትዮጵያ የመጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ጠቅላይ ጸሐፊ
ክቡራን የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያ ኃላፊዎችና የየድርጅቶች ሥራ አስኪያጆች፤
ክቡራን የአህጉረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጆችና የስብከተ ወንጌል ክፍል ኀላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
👉 መርሐግብሩ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የሸገር ከተማና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ሲሆንሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም የበላይ ኀላፊ መሪነት የመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ካልናት ጸሎተ ወንጌል አድራሽነት ተጀምሮ የስብከተ ወንጌል ተግዳሮቶችና መፍትሔዎቻቸው በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ ቀርቦ በርሱም ላይ ወይይት ተደርጎ ከምሳ ሰዓት በፊት ያለው መርሐግብር ተጠናቋል።