ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል በቃሊቲ አካባቢ ለበጎ አድራጎት ሥራ ከ23 ዓመት በፊት ያስገነቡትን Gተ1 የመኖሪያ ሕንጻ ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ሕሙማን መርጃ ማኅበር በስጦታ አበረከቱ

ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል የዋሽንግተን እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሰጡት የስጦታ መርሐ ግብር ላይ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተገኝተዋል።
ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ለበጎ አድራጎተት እንዲውል የሕንጻ ቁጥሩ 982 የሆነውንና በግል ገንዘባቸው በ544 ካሬ ሜትር ቦታ ያረፈ ሕንጻ በመገንባት ለዚሁ ዓላማ እንዲውል አድርገዋል።
ሕንጻው ያረፈበት ቦታ 240 ካሬ ሜትር ሲሆን በግንባታ ወቅት የወጣበት ወጪ ከ3ሚሊዮን በላይ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ባለው የገበያ ዋጋ ከ120 ሚሊዮን በላይ ይገመታል።ሕንጻው ከተገነባ 23 ዓመታትን ማስቆጠሩ ተገልጿል።
በመርሐ ግብሩ አቶ አምሓ ይልማ ባቀረቡት መልእክት ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ሕንጻውን በገነቡበት ወቅት ያስተላለፉትን በሕግ ፊት የሚጸና ተብሎ የተመዘገበውን የኑዛዜ ሰነድ በጽሑፍ አቅርበውታል።
ቤቱን ለመቄዶንያ አረጋውያንና አእምሮ መርጃ ማዕከል ለማስተላለፍ ከቤተ ሰብ ጭምር ኮሚቴ (ቦርድ) ተቋቁሟል ተብሏል።
በመቀጠልም በስጦታ አድራጊ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤልና በስጦታ ተቀባይ መቄዶንያ የውል ስምምነት ሰነድ እና ካርታ ርክክብ ተፈጽሟል።
ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል በስጦታ መርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልእክት እግዚአብሔር የሰጠኝን ቤት ለእግዚአብሔር አስረክቤያለሁ ብለዋል። ብፁዕነታቸው ጨምረው እንደገለጹት 19 ዓመት የቤቱ ኪራይ ለበጎ አገልግሎት ውሏል ብለዋል።
መስጠት የማይፈልጉ ኃይሎች የእኔን ስጦታ ሲተቹ ሰምቻለሁ።
ይህ ግን አግባብነት የለውም ብለዋል። ብፁዕነታቸው እኔ የሚቆጠር ንብረት የለኝም ያሉ ሲሆን በመጨረሻም ካርታውንና የቤቱን ቁልፍ የመቄዶንያ መሥራች ብኒያም በለጠ ተረክበው የምስጋና መልእክት አስተላልፈዋል።
ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል 18 ዓመታቸው ስለመነኮሱ እግዚአብሔር የመቄዶንያ መሥራች ብንያም በለጠ የጠራቸው አባት መሆናቸውን እናምናለን። ስጦታቸውን የሚያጣጥሉ ኃይሎች መፈጠራቸው አሳዝኖናል ብለዋል።
ቀድሞም የቤት ኪራዩን ሜቄዶንያ ሲጠቀምበት የቆየ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ቤቱ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል 58ኛ መቄዶንያ ቅርንጫፍ እንዲባል ጠይቀዋል።
በመቄዶንያ ታሪክ ትልቁ ስጦታ ይህ ነው በማለት የመቄዶንያ መሥራቹ ብኒያም በለጠ ተናግረዋል።
በመቀጠልም የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች ስለስጦታው አርአያነት ያለው ነው በማለት አድናቆታቸውን ገልጸዋል።
የመቄዶንያ አረጋውያንና አእምሮ ሕሙማን ማዕከል ተረጅዎችም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ አባታዊ ትምህርት የሰጡ ሲሆን ብፁዕነታቸው በሰጡት ትምህርት የትንሣኤው በኩር የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ከእኔ ተማሩ በማለት ያስተማረውን ትምህርት ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል በተግባር አውለውታል ብለዋል።
ብፁዕነታቸው ራሳቸውን በመስጠት ትልቁን መሰናከል አልፈዋል ብለዋል። ዛሬ ያጣነው የሚሠራ እንጂ የሚያወራ አይደለም ሲሉ መልዕታቸውን አጠቃለዋል።
በመጨረሻም በብፁዕ አቡነ ኤልያስ የኖርዲክ ሀገራት እና የግሪክ አህጉረ ስብከት ሊቀጳጳስ የመጨረሻ ትምህርትና ጸሎት መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።©Eotc tv.