የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና የኢትዮጵያ ፈደራል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ “ጠንካራ ትብብር ለሀገር ሰላም! ሰላም የወል ሀብታችን ነው!” በሚል መሪቃል ስለሰላም በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸውን የጋራ ስምምነት ተፈራረመ
ግንቦት 4 ቀን 2018 ዓ.ም
ከየቤተ እምነቱ የተወከሉ አባቶች በተገኙበት “ጠንካራ ትብብር ለሀገር ሰላም በሚል የተከናወነው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እና የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ የጋራ ስምምነት ፊርማ ፤ በሀገራችን በሚከናወኑ ምክክሮች ሰላምን ለማረጋገጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት መሆኑ ተገልጿል ።
የስምነት ስነዱን የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሰብሳቢ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ እና የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ተፈራርመዋል ።
በዚሁ ስምምነት ውስጥ ወንጀለኞችን መከላከል ፣ በጋራ በመሆን ወንጀል ሳይፈጠር አስቀድሞ መከላከል የሚያስችል አቅም መፍጠር ፣ በሕግ ገደብና ነጻነት አንዱ በሌላው ጣልቃ ሳይገባ፣ የእምነት ተቋማት እና የሕግ አስከባሪው አካል በየራሳቸው የሕግ ማዕቀፍ እንዲሠሩ ድንበር የለየ መሆኑ ተገልጿል ።
ሚስጥራዊነት በጋራ ስራዎች ወቅት የሚገኙ መረጃዎችና በመድረኩ መልዕክት ያስተላለፉ ንቡረ ዕድ ኤልያስ አብርሃ የመንበረ ፓትርያርከሰ ጠቅላይ ቤተክህነት የመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ “እግዚአብሔር የሚናገረውን እሰማለሁ፥ ሰላምን ለሕዝቡና ለቅዱሳኑ ይናገራልና” የሚለውን ቃል በመጥቀስ፣ ቤተክርስቲያን ሁልጊዜ ስለ ፍጻሜውም ሰላም እንደምትጸልይ ገልጸዋል ።
ሼህ ኢብራሂም ቱፋ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ” ሰላም እንዲመጣ የሃይማኖት ሕግጋትን በማክበር እያንዳንዱ አማኝ የእምነቱን አስተምህሮ እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተክርስቲያናት ካውንስልን በመወከል ንግግር ያደረጉት ቄስ ደረጀ ጅምበሩ የክርስትና እምነት ዓላማ ሰላምን ማጽናት ፣ እንደሆነ ገልጸው መጽሐፍ ቅዱስ ለሰላም ወሳኝ እንደሆነ አስገንዝበዋል ።
ይህ የጋራ ስምምነት ሀገራችንን ሰላምና ደኅንነት በመጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ላይ ለማቆም ትልቅ ሚና እንደሚኖረው ተወስቷል።© EOTC t.v