በአዶላ ወዩ በሚገኙ አድባራት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ከ1ኛ እስከ 3ኛ ክፍል ለሚማሩ ደቀመዛሙርት አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተሰጠ
ግንቦት 10ቀን 2018ዓ.ም
በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በኩል ተዘጋጅቶ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት፣ በብፁዕ አቡነ ዜናማርቆስ የጉጂ ቦረና ሊበን እና የምዕራብ አርሲ አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መመሪያ መሠረት በሁለቱም አኅጉረ ስብከቶች ተግባራዊ እየሆነ መሆኑ ተገልጿል።
በግንቦት 09 ቀን 2018 ዓ.ም በአዶላ ወዩ ለሚገኙ አድባራት የሰንበት ትምህርት ቤት ደቀመዛሙርት የተሰጠው ሥልጠና፣ በወረዳው ዋና ጸሐፊና በደብረገነት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን ስብከተ ወንጌል ክፍል ኃላፊ ላዕከ ወንጌል ወሰን የለው ባሕሩ ተሰጥቷል።
በመርሃ ግብሩ “በሰንበት ትምህርት ቤት እና አብነት ተማሪዎች ላይ በትኩረት እንሥራ” በሚል መሪ ቃል የተካሄደ ሲሆን፣ የወረዳው ዋና ሥራ አስኪያጅና የደብረብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ መጋቤ ተአምር ሃይማኖት ደኖ በተገኙበት አባታዊ ምክርና መመሪያ ተሰጥቷል።
በዕለቱ ከተለያዩ አድባራት የመጡ በርካታ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች በፕሮግራሙ ላይ መሳተፋቸውን በመግለጸሰ ዘገባውን ያደረሰን የሀገረ ስብከቱ ጽሕፈት ቤት ነው።