የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ደንበኛ ተኮር ስርዓት የወለደው የነዋሪዎች አንድነት ከድርጅቱ አልፎ ከጠቅላይ ጽ/ቤቱ ጋርም እያስተሳሰረ መሆኑ ተገለጸ

May 23, 2026

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት የተጀመረው ደንበኛ ተኮር ስርዓት ደንበኞችን ከድርጅቱ ጋር ከማቆራኘት አልፎ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጋር መናበብን የፈጠረ ሲሆን ይህንኑ በሚገልጽና ተባባሪነትን በሚያሳይ መልኩ በዛሬው እለት የጽዳት ዘመቻ አካሂዷል።
የጽዳት ዘመቻው ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም የበላይ ኀላፊ፤ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ የቅርሳቅርስ ፣ ቤተመጻሕፍትና ወመዘክር ፣ የማኅበራት ፣ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያዎች የበላይ ኀላፊ፣ ሊቀ ስዩማን እስክንድር ገብረ ክርስቶስ የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅና የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊና የመንትዮች ሕንፃ ነዋሪዎች በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን ወደፊት በሁሉም ሕንፃዎች እንደሚካሄድ ይጠበቃል።
ይህ የጽዳት ዘመቻ ከአከራይና ተከራይ ትስስር ባለፈ በባለቤትነት ስሜት እንዲገለገሉ የሚያቀራርብና ወደፊትም በትብብር ቤተክርስቲያንን ለማገልገል የሚረዳ እንዲሁም ነዋሪዎች ለኑሮ የሚመርጡት ሥፍራ ምቹ ፣ ጽዱና ማራኪ ሕንጻዎች እንዲሆኑ የሚያደርግና የሚያግዝ በመሆኑ በየወሩ መካሄድ እንዳለበት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አባታዊ መመሪያ ሰጥተዋል።
የብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ጸሐፊምው በበኩላቸዉ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት በዋናው መሥሪያ ቤት እየተከናወነ የሚገኘው ቅጥር ጊቢውን የማስዋብ ሥራ ወደ ውጭ ወጥቶ የድርጅቱ ደንበኞች በሚገኙበት ሁሉ መቀጠል እንዳለበት ሲያሳስቡ ቤተክርስቲያን የንጽሕና አዳራሽ ናት ። ንጽሕና የክርስትና ዋና መገለጫ ነው። ይህንን ማድረግ ክርስትናን መግለጽ ሲሆን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የፈነጠቀው የልማት ጀምበር በሁሉም ሕንጻዎች መካሄድ ይኖርባቸዋል ብለዋል።
በተለይም የድርጅቱ ደንበኞች እስካለሁ እኖራለሁ በሚል ጠባብ አስተሳሰብ ውስጥ እንዳይገቡና በባለቤትነት ስሜት የተከራዩትን ቤት በአግባቡ በመጠቀም ትብብራቸውን እንዲያሳዩ ጠቁመዋል።
በመጨረሻም የሁሉም ሕንፃ ነዋሪ ኮሚቴዎች በየጊዜው ይህንን የጽዳት ዘመቻ ለመካሄድ ዝግጅት እያደረጉ ሲሆን በዘሬው እለትም የጽዳት ዘመቻ ያደረጉት የመንትዮች ሕንፃ ነዋሪዎችና ኮሚቴዎች ባደረጉት ሥራ ፈር ቀዳጅ በመሆናቸው ተመስግነው በብፁዕነታቸው ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ ተጠናቋል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/000042.jpg 252 448 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-05-23 13:15:222026-05-23 13:15:22ደንበኛ ተኮር ስርዓት የወለደው የነዋሪዎች አንድነት ከድርጅቱ አልፎ ከጠቅላይ ጽ/ቤቱ ጋርም እያስተሳሰረ መሆኑ ተገለጸ
Search Search

Recent Posts

  • የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም 81ኛ ዓመት የአንድነት ኑሮ ምሥረታ ክብረ በዓል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከብረ
  • የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ በአዲስ አበባ የሰላምና የያብሮነት የጸሎት መርሐ ግብር ” ሃይማኖታዊ እሴቶቻችን ለዘላቂ ሰላማችን ” በሚል መሪ ቃል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የሌሎች ሃይማኖት ተቋማት ተወካዮች በተገኙበት አደረገ
  • የአዳማ ደብረ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምህረት ካቴድራል 1ኛ ዓመት የቅዳሴ ቤት ክብረ በዓል ብፁዕ አባታችን አቡነ ጎርጎርዮስ በተገኙበት ተከበረ
  • በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ተከበረ
  • ደንበኛ ተኮር ስርዓት የወለደው የነዋሪዎች አንድነት ከድርጅቱ አልፎ ከጠቅላይ ጽ/ቤቱ ጋርም እያስተሳሰረ መሆኑ ተገለጸ

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቡራኬ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከናወነ Link to: በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቡራኬ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከናወነ በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት... Link to: በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ተከበረ Link to: በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን ቅዳሴ ቤት ተከበረ በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የለገጣፎ ኆኅተ ገነት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top