የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ከግንቦት እስከ ግንቦት ክፍል ሦስት

May 26, 2026

ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ሆነው እንዲሠሩ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በከፍተኛ ድምጽ ከተሾሙበት ጊዜ ጀምሮ የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ደረጃውን
በጠበቀና የቅዱስ ሲኖዶስን ክብር በሚመጥን መልኩ እንዲደራጅ ፣ እንዲጸዳና እንዲዋብ በማድረግ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ምንም ዓይነት ወጪ ሳይጠይቁ በጎ አድራጊ ምዕመናንን በማስተባበር የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት ያማረና ግሩም እንዲሆን አድርገውታል።
ይህም በመሆኑ ጽሕፈት ቤቱ አገልግሎቱን በተደራጀና በተቀላጠፈ አግባብ ማከናወን የሚችልበትን ሁኔታ መፍጠር ከመቻላቸውም በላይ መደበኛና ከመደበኛ ውጪ በሆነ መልኩ የቅዱስ ሲኖዶስን ሥራ የሚያግዙ ምሁራን የሥራ ኃላፊዎችን በማሳተፍ የቅዱስ ሲኖዶስ ቃለ ጉባኤ በአግባቡ እንዲጻፍ፣የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እንዲዘጋጅና ወጥነት ያለው የመረጃ መለዋወጫ ሥርዓት እንዲዘረጋ በማድረግ የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔዎች ተከትሎ ግልጽነት እንዲፈጠር በማድረግ የቅዱስ ሲኖዶስን ክብር የሚመጥኑ በርካታ ሥራዎችን ማከናወን ችለዋል።
ብፁዕነታቸው የቋሚ ሲኖዶስ ስብሰባዎች በሚደረጉበት ጊዜ ተቋማዊ መሰረታቸውን የበለጠ አጠናክረው የሚከናወኑበትን ሥርዓት በመከተል፣ቅዱስነታቸው በጤና እክል ምክንያት የቋሚ ሲኖዶስን ስብሰባ በማይመሩበት ጊዜ ቅዱስነታቸውን በመወከል የቋሚ ሲኖዶስ ስብሰባን በአግባቡ በመምራት ወቅታዊ መረጃዎችን ለቅዱስ ፓትርያርኩ በማስረዳትና ከቅዱስነታቸው መመሪያን ተቀብለው በአፋጣኝ በመተግበር የተዋጣለት ሥራን ሠርተዋል።በእነዚህ ጊዜያትም የቅድስት ቤተክርስቲያንንና የብፁዓን አባቶችን ክብር በማስጠበቅ ተቋማዊ ውሳኔዎችን በማስወሰንና አፈጻጸማቸውን በየወቅቱ በመከታተል አርዓያነት ያለው ሥራን ሠርተዋል።
ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው በዘመነ ሢመታቸው የተከናወኑ ሁለት ጉባኤያትን በአግባቡ በማስተባበር፣በመምራትና ሲኖዶሳዊ ክብርን የሚያስጠብቅ ማጠቃለያን በማቅረብ፣እጅግ የተረጋጋ፣ፍጹም መደማመጥ የታየበት ውጤታማ ጉባኤ እንዲካሔድ በማድረጋቸው የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የተሰማቸውን ደስታ በምስጋና ገልጸውላቸዋል።ለዚህ ውጤታማነታቸው ትልቁ ምክንያትም ብፁዕነታቸው ያላቸው የረጅም ጊዜ የሥራ ልምድ፣ብልሃት የተሞላበት የመሪነት ክህሎት፣አርቆ የማሰብ ብቃት፣መጠነ ሰፊ ተቋማዊ አመለካከት፣ ለቤተክርስቲያን ሉዓላዊነት እና ክብር በቆራጥነት የመሥራት የዳበረ ልምድና ፍጹም የሆነ የሁለንተናዊ ብቃት ባለቤት መሆናቸው እንደሆነ የሚጠራጠር አይደለም።
ከፍ ሲል በተጠቀሱት ዋናዋና ምክንያቶችም የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት የአንድ ዓመት የሥራ አፈጻጸም እጅግ ስኬታማና የተዋጣለት መሆን ችሏል።
ከግንቦት እስከ ግንቦት በቤተክርስቲያናችን ደረጃ የተመዘገቡት ውጤቶች እጅግ በአጭሩ በሦስት ክፍል የተመለከትናቸው ሲሆኑ የተመዘገቡት ውጤቶች ሊመዘገቡ የቻሉት አልጋ በአልጋ በሆነ የማስፈጸምና የመፈጸም ሂደት አልነበረም።ይልቁኑ በርካታ እሾህና አሜኬላ ታልፎ እንጂ፤በቤተክህነት ታሪክ ታይቶና ተሰምቶ የማያውቅ ውጤት የተመዘገበውም ሁለቱ ብፁዓን አባትች በርካታና እልህ አስጨራሽ ተግዳሮቶችን በድል እድራጊነት ተወጥተው እንደሆነም ብዙ ማሳያዎችን መደርደር ይቻላል።
ከሁሉ የከፋውና አሁን ድረስ ልዩልዩ ሥልቶችን በመቀየር እየተሞከረ የሚገኘው ታላቁ ተግዳሮት ሁለቱን አባቶች ለመለያየት እየተደረገ ያለው ያልተሳካና ሊሳካ የማይችለው ሙከራ ሲሆን መሰረታዊ ምክንያቱ አሁን የተመዘገበውና ወደፊት የሚመዘገበው ውጤት እንዴት በሁለቱ አባቶች ዘመነ ሢመት ይሆናል? ከሚል ቤተክህነታዊ ቅንአት የሚነሳ ሆኖ መዳረሻው ዘረኝነትን በማስፋፋት ቤተክርስቲያንን የፖለቲካዊ ፍላጎቶች ማስፈጸሚያ መድረክ ማድረግን መሰረት ያደረገ ሆኖ ከሀገር ውስጥ እስከ ውጪ በተደራጀ መልኩ የሚከወን እኩይ ተግባር እንደሆነም ግልጽ ነው።
ይህ በደንብ የገባቸውና የዚህ እኩይ ዓላማ አስፈጻሚዎች እነማን እንደሆኑ ጠንቅቀው የሚያውቁት ብፁዓን አባቶቻችን እነዚህ እኩያን በሁለቱ መካከል የሚገቡበት ቀዳዳ እንዳይኖር በማድረግና በዋና ሥራቸው ላይ ብቻ በማተኮር ባደረጉት እንቅስቃሴ የሚታይና የሚዳሰስ ውጤትን ሲያስመዘግቡ በሌላ በኩል ደግሞ የነዚህን እኩያን ፍላጎት ማምከን ችለዋል።
ይሁን እንጂ ሁለቱን ካላለያዩ፣በመካከታቸው መለያየትን ካልፈጠሩ፣ ፓለቲካዊ ዓላማቸውን ማስፈጸም እንደማይችሉ የተገነዘቡት የቤተክህነቱ ተግዳሮት ጠንሳሾች አንድ ጊዜ የፌስቡክ ሰራዊት በማደራጀትና የሐሰት ስም ማጥፋት ላይ በመሰማራት፣ ሌላ ጊዜ የአንደኛው አባት ተቆርቋሪ በመምሰልና የሐሰት ፕፖጋንዳን መሰረት ያደረገ ዘመቻን በመዝመት፣ሲያሻቸው ደግሞ የሚቀርቧቸውን አባቶች በማሳመንና አንዱ በአንዱ ላይ ጥርጣሬን በመፍጠር ወደ ጸብ እንዲገቡ በመጎትጎት፣ሲቀጥሉ ደግሞ የሁለቱ አባቶች ቀራቢ ናቸው የሚባሉ ሰዎችን በጥቅማጥቅም በመደለል እሱ አልሳካ ሲላቸው ደግሞ በነዚሁ ወገኖች ላይ ጠላቶችን በማደራጀት እንዲነሱባቸውና እንዲወነጀሉ በማድረግ፣ ሲጨንቃቸው የነሱ ተከታዮች በመሆን አባቶችን እንዲክዱ በማግባባት ሲብሰ ደግሞ ሁለቱን አባቶች በንዋይ በመደለል አንድነታቸውን ለማናጋት ብዙ ቢጥሩም የሁለቱ ብፁዓን አባቶች የኖረና ሦስት አሥርታትን የዘለቀ ወንድማማችነትን መናድ ሳይችል በመቅረታቸው እነሆ በፍቅርና በአንድነት ከግንቦት እስከ ግንቦት በስኬት መዝለቅ ችለዋል።
ለወደፊትም አንድነታቸውን አጽንተው፣ወንድማማችነታቸውን አሳድገው፣በርካታ ውጤቶችን አስመዝግበው ፣የቤተክርስቲያንን
ጥቅም አስከብረው፣ የጠቅላይ ቤተክህነቱን አሰራር አዘምነው፣ ለትውልድ የሚተላለፍ ታሪክ ጽፈው፣በጥቅሉ ቤተክርስቲያንን ለመበተን መከራ የሚበሉ ሕልመኞችን ፍላጎት አክሽፈው ቀሪ ዘመነ ሢመታቸውን ከአሁን በበለጠ አንድነትና ፍቅር በመፈጸም የቤተክርስቲያንን አስተዳደራዊ ትንሳኤን እንደሚያበስሩ ጥርጥር የለውም።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ግንቦት ፳፻ ፲ወ፰ ዓ.ም
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr000.jpg 442 336 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-05-26 10:28:442026-05-26 10:28:44ከግንቦት እስከ ግንቦት ክፍል ሦስት
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም 81ኛ ዓመት የአንድነት ኑሮ ምሥረታ ክብረ በዓል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከብረ Link to: የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም 81ኛ ዓመት የአንድነት ኑሮ ምሥረታ ክብረ በዓል ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ተከብረ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም 81ኛ ዓመት... Link to: ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው Link to: ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top