የቤቶችና ሕንጻዎች ልማት ድርጅት ሠራተኞቹን አመሰገነ።
ሰኔ 22 ቀን 2018 ዓ.ምበመርሐግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ክርስቲያናዊ ልማትና ተራድኦ ኮሚሽን እና የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት የበላይ ሊቀ ጳጳስ ሊቀ ሥዩማን እስክንድር ገብረ ክርስቶስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ዋና ኃላፊ እና የቤቶችና ሕንጻዎች ልማት ድርጅች ዋና ሥራ አስኪያጅ እንዲሁም የድርጅቱ ልዩ ልዩ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ተገኝተዋል::
በመርሐግብሩ በተቋሙ የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ የተቋሙ ሠራተኞች የምሥጋናና የዕውቅና መርሐ ግብር የተከናወነ ሲሆን ለሠራተኞቹ በብፁዕ አቡነ ሳሙኤልና በሊቀ ሥዩማን እስክንድር ገ/ክርስቶስ አማካኝነት የምሥጋና የምሥክር ወረቀት ተሰጥቷል።
ሊቀ ሥዩማን እስክንድር ገ/ክርስቶስ በመሥጋና እና በዕውቅና መርሐግብሩ ላይ ድርጅቱ ላስመዘገባቸው ውጤቶች የድርጅቱ ሠራተኞች እጅግ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክታችኋል በዚህም ለትጋታችሁ እና ለጽናታችሁ በድርጅቱ ስም እያመሰገንኩኝ ወደፊትም ለሚኖረን ቆይታ በከፍተኛ የሥራ ኃላፊነት እራሳችሁን እንድታዘጋጁና ሥራችሁን በኃላፊነትና በታማኝነት እንድትሠሩ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

አክለውም ከዚህ ቀደም ድርጅቱ የመጣባቸው የአሠራር ክፍቶች አሁን ላይ የማይቀጥልና ሁሉም ሠራተኛ ሥራውን በአግባቡ መሥራት እንዳለበት እንዲሁም የምሥጋና መርሐ ግብሩ እንዳለ ሆኖ የአሠራር ክፍተት የሚታይባቸው ሠራተኞች አስተዳደራዊ እርምጃ እንደሚወሰድበት ጠቅሰው በቀጣይ ዓመት ድርጅቱ እራሱን እና አሠራሩን በቴክኖሎጂ በማዘመን ዘመኑን የዋጀ እና የተቀላጠፈ አገልግሎት የሚሰጥበትን ከፍተኛ ሥራዎች የምናከናውንበት ነው ብለዋል።
ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል በመርሐ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት እንዲ አይነት የዕውቅናና የምሥጋና መርሐ ግብራት የሠራተኛውን የሚያቀራርቡ ለተሻለ ሥራ የሚያተጉ ከመሆናቸው ባሻገር ጥሩ የአመራር ጥበብ የታየበት ነው ያሉ ሲሆን ይሄ ተግባር የአንድን ድርጅት የማዘመንና የማሳደግ ውጤት ጉልህ ማሳያ ነው ፤ አሁን የተሸለማችሁ በቀጣይ የተሻለ ውጤት በማምጣት ራሳችሁንም ተቋማችሁን ማሳደግ መለወጥ ይገባችኋል፤ በዚኛው ዙር ያልተሸለማችሁ የተቋሙ ሠራተኞች በቀጣይ በሥራችሁ በመትጋትና በመለወጥ በቀጣይ ዓመት የተሻለ ውጤት በማምጣት እንድትሸለሙ ሲሉ አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በመጨረሻም የእውቅናና የምሥክር ወረቀት የተሰጣቸው የድርጅቱ ሠራተኞች ለተደረገላቸው እውቅናና ምሥጋና መደሰታቸውን ገልጸው በቀጣይ ተቋሙን አሁን ካለው በተሻለ በትጋትና በታማኝነት እንደሚያገለግሉ ቃል ገብተዋል።
መርሐ ግብሩ በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ክርስቲያናዊ ተራዶኦ ልማት ኮሚሽንና የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት የበላይ ሊቀ ጳጳስ በጸሎት ተጠናቋል።© EOTC TV