የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የ ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የጥምቀት በዓል በሰላም ተከብሮ መዋልን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ ፤

January 19, 2023

የ ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የጥምቀት በዓል በሰላም ተከብሮ መዋልን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ ፤
******

ጥር ፲፫ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
አዲስአበባ ኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየ ዓመቱ ጥር፲ ና ፲፩ቀን የሚከበሩት የከተራና የጥምቀት በዓላት ዘንድሮም በታላቅ ሃይማኖታዊ ሥነሥርዓት ተከብረው ውለዋል።ይህ በቤተክርስቲያናችን የሰላም፣የስምምነት ፣የአንድነትና የመከባበር መገለጫ የሆነው በዓላችን ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መልኩ ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ከበዓሉ ቀድሞ ዐቢይ ኮሚቴ በማቋቋም በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል።

የተቋቋመው ዐቢይ ኮሚቴም ንዑሳን ኮሚቴዎቻችን በማደራጀት በየተመደበበት ኮሚቴ ውጤታማ ሥራዎችን አከናውኗል።ይህም በመሆኑ በልዑል እግዚአብሔር ረድኤትና በረከት ስኬታማ በዓል ለማክበር ችለናል።

በተለይም የጠቅላይ ቤተክህነትና የመንግስት የጸጥታ አካላት ያደረጉት የተጣመረ እንቅስቃሴ ለበዓሉ ድምቀትና ማማር እንዲሁም ሰላማዊ በሆነ መልኩ መከበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደነበረው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያናችን ትገነዘባለች።

ለዚህ ስኬታማ የበዓል አከባበር ቤተክርስቲያናችን ከበዓሉ ቀደም ብላ ከካህናት፣ከወጣት የቤተክርስቲያናችን ልጆችና ኦርቶዶክሳዊ ከሆኑ የሚዲያ ተቋማት ጋር ያደረገቻቸው ውጤታማ ውይይቶች በእርግጥም ተነጋግሮ፣ተመካክሮና ተናቦ መስራት ለውጤት የሚያበቃ መሆኑን ያረጋገጡ ናቸው።ይህ አይነቱ የመመካከር ፣የመወያየትና ተናቦ የመስራት ተግባርም ለወደፊቱ ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል።

ሕዝበ ክርስቲያኑ በተለይም ደግሞ ወጣት ልጆቻችን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በበዓል አከባበሩ ዙሪያ በተደጋጋሚ በሚዲያዎች ያስተላለፈቻቸውን መልዕክቶች በመቀበል በዓሉ የቤተክርስቲያያችንን ክብር በሚመጥን መልኩ ተከብሮ እንዲውል በማድረግ ረገድ ያሳያችሁት ሃይማኖታዊና መንፈሳዊ ጨዋነትን የተላበሰ የበዓል አከባበር ሥርዓት የሚደነቅና ተጠናክሮ መቀጠል የሚገባው ነው።
በዚህም ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን የተሰማትን ደስታ ትገልጻለች።

በማዕከል ደረጃ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖትት፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ሚኒስትሮች፣ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤና ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት በተገኙበት በጃንሜዳ ባህረ ጥምቀት የተከበረው በዓልም እጅግ ባማረና በደመቀ መልኩ ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደርና ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ ቅዱስነታቸው እና የክብር እንግዶች በዓሉን ያከበሩበትን ስቴጅና ሳውንድ ሲስተም ከነ ሙሉ ግበዓታቸው እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ ድንኳኖችን በማቅረብ ለበዓላችን ድምቀትና ማማር ትልቁን አስተዋጽኦ በማበርከት የሚያስመሰግን ተግባር ፈጽመዋል፤ለዚህም ቤተክርስቲያናችን ልባዊ ምስጋናዋን ታቀርባለች።

በአጠቃላይ በዓላችን በድምቀት ተከብሮ መዋል እንዲችል የደከማችሁ አካላት ሁሉ ልዑል እግዚአብሔር የድካማችሁን ዋጋ እንዲከፍላችሁ ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያናችን የዘወትር ጸሎቷ ነው።

በተለይም በዓሉ ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መልኩ ተከብሮ መዋል ይችል ዘንድ ሌት ከቀን ስትደክሙ የሰነበታችሁ የጸጥታና ነደህንነት የጋራ ግብረ ሃይል አባላት ድካምና ልፋታችሁ ፍሬ አፍርቶ በዓሉ በሰላም ተከብሮ በመዋሉ ቅድስት ኦሮቶዶሳዊት ቤተክርስቲያናችን የተሰማትን ደስታ ከታላቅ መንፈሳዊ ምስጋና ጋር እየገለጸች እግዚአብሔር አምላክ ሥራችሁን ሁሉ እንዲባርክና የዘወትር ጥበቃው እንዳይለያችሁ አጥብቃ እንደምትጸልይላችሁ ትገልጻለች።

ከበዓሉ በፊት በዓሉን በተመለከተ የቤተክርስቲያናችንን መልዕክት በማስተላለፍ፣በበዓሉ ወቅትም የበዓል አከባበር ሥርዓቱን ለመላው ዓለም በቀጥታና በዜና ሥርጭት በመዘገብ ላይ ለሰነበታችሁ የሚዲያ ተቋማትና ጋዜጠኞችም ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ልባዊ ምስጋናዋን እያቀረበች ሥራችሁ ሁሉ የተሳካና ውጤታማ እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞቷን ትገልጻለች።

በነገው እለት ወደየ አብያተክርስቲያናቱ የሚገቡት ታቦታትም ልክ እንደዛሬው የበዓል አከባበር ሥነሥርዓት ፍጹም ሰላማዊና ደማቅ በሆነ በመልኩ ይከብሩ ዘንድ ሕዝበ ክርስቲያኑ በተለይም ወጣት ልጆቻችን ታቦታቱ በሰላም ወደየ መንበረ ክብራቸው እንዲመለሱ ቤተክርቲያን ባስተማረቻችሁ የመተሳሰብ፣የመደጋገፍና የመከባበር ሥርዓት መሰረት የሚጠበቅባችሁን ሃይማኖታዊ ግዴታ እንድትወጡ ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያናችን መልእክቷን ታስተላልፋለች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት

ጥር ፲፩ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
አዲስአበባ ኢትዮጵያ

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/favicon.png 169 151 tc https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg tc2023-01-19 19:04:242023-01-19 19:04:24የ ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የጥምቀት በዓል በሰላም ተከብሮ መዋልን አስመልክቶ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት የተሰጠ መግለጫ ፤
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ፎቶ ሪፖርታዥ፦ የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የጥምቀት በዓል አከባበር Link to: ፎቶ ሪፖርታዥ፦ የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የጥምቀት በዓል አከባበር ፎቶ ሪፖርታዥ፦ የ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም የጥምቀት በዓል... Link to: የጋምቤላ የጥምቀት በዓል አከባበር Link to: የጋምቤላ የጥምቀት በዓል አከባበር የጋምቤላ የጥምቀት በዓል አከባበር
Scroll to top Scroll to top Scroll to top