የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ቅዱስነታቸው በትግራይ የሚገኙ አባቶች ችግሩን በጠረጴዛ ዙሪያ በሚደረግ ውይይት እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ

July 10, 2023

ሐምሌ ፫ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም
“”””””””””””””””””””””””””

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በክልል ትግራይ በጦርነቱ ምክንያት ለተፈናቀሉ ወገኖች ርዳታ ለመስጠትና በትግራይ ከሚገኙ አባቶች ጋር የተፈጠረው ችግር በውይይት ለመፍታት ዛሬ ፣ ሐምሌ ፫ቀን ፳፻ ፲ወ፭ዓ.ም ማለዳ መቐለ ከተማ ገብተዋል።

በቅዱስነታቸው የሚመራው የሰላም ልዑክ ቡድን መቐለ ሲደርስ በክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት አቀባበል የተደረገለት ሲሆን፤ በክልሉ ጽሕፈት ቤትም ከአቶ ጌታቸው ረዳ የጊዜያዊ መንግስቱ ርዕሰ መስተዳር ጋር ተወያይተው የሃያ ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርገዋል።

ቅዱስ ፓትርያርኩ ከክልሉ ጊዜያዊ መስተዳድር ፕሬዚዳንት ጌታቸው ረዳ ጋር በሰጡት የጋራ መግለጫ በትግራይ የሚገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የተፈጠረውን ችግር ወደ ጠረጴዛ መጥተው በውይይት እንዲፈቱ አባታዊ ጥሪ አስተላልፈዋል።

በዚሁ ጊዜ ቅዱስነታቸው እንደገለጹት ሁኔታው አስከፊ ቢሆንም የመጣነው ለመወያየት ነው፤ ቅዱስ ሲኖዶስ በአሁኑ ጉባኤ ይቅርታ ጠይቋል።ይህ ከሆነ መወያየት ጥሩ ነው ብለን መጥተናል።

መወያየት ክፉ አይደለም ። ሰው አሳቡን ለመግለጽም ሆነ ለመስማማትና ላለመስማማት መገናኘትና መወያየት ክፉ አልነበረም ብለዋል።

መቼም ብፁዓን አባቶች በምን ምክንያት እንደቀሩ እኛ የምናውቀው ነገር የለም ያሉት ቅዱስ ፓትርያርኩ በጤና ነው ወይስ አውቀው ነው ሳያውቁ ነው አምነውበት ነው ሳያምኑበት ነው የቀሩት የሚለውን እኛ የምናውቀው ነገር የለም ብለዋል።አያይዘውም ቅዲስነታቸው፤ መወያየት ጥሩ ነበር። በመወያየት አሳብን መግለጽ ይቻላል። የደረሰውን ችግር መግለጹና ማስረዳቱ አንድ ቁም ነገር ነበር። ይሁንም አይሁንም ለማለት ውይይት ጥሩ ነበር ።የሆነው ሆኖ አልተገኙም በማለት በክልሉ የሚገኙ አባቶች በውይይቱ አለመገኘታቸውን ገልጸዋል ።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ቅዱስነታቸው በመቐለ ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና ወደ ሚገኘው ቅዱስ ሚካኤል ደብር ለጸሎት ቢያመሩም፤ የቤተ ክርስቲያኑ በር ተዘግቶባቸው ቅዱስነታቸውና የመሩት የሰላም ልዑክ በር ላይ ጸሎት ለማድረስ ተገድዷል። ድርጊቱም የቅዱስነታቸውን ድምፀ ግፉዓን መሆናቸውን ከግምት ውስጥ ከአለማሰገባቱም በላይ አሳዛኝ የታሪክ ጠባሳ ሆኖ አልፏል።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ መንግሥት ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በበኩላቸው ቤተ ክርስቲያን ዘግይታም ቢሆን ተጎጂዎችን ለመጎብኘትና ከብፁዓን አባቶች ጋር ለመወያየት ልዑካን መላኳ ተገቢ መሆኑን ገልጸው፤ጉዳዩ በውይይት መፈታት እንዳለበት እናምናለን ብለዋል። አያያይዘውም ይሄ ነገር አንድ እምነት በሚከተሉ ወንድማማቾች ዘንድ አንድ ማኅበር ውስጥ ባሉ ዘንድ የሚፈጠር ልዩነት በምክክር ነው መፈታት ያለበት ግን እንደ መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አንገባም።

በሃይማኖት መካከል ጣልቃ አንገባም ማለት በእንደዚህ ዓይነት ምክንያቶች የሚፈጠሩ ልዩነቶች የሚፈጥሯቸው ጣጣዎች አይመለከቱንም ማለት ግን አይደለም ብለዋል።
የልዑካን ቡድኑ በትግራይ የሚገኙ ተፈናቃዮችን የጎበኙ ሲሆን ፤በነገው ዕለትም በጉዞው ዙሪያ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለትግራይ ክልል የ20 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገች Link to: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለትግራይ ክልል የ20 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን... Link to: ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁን በተመለከተ በትግራይ ተፈናቃዮች የተደረገው መሰረተ ቢስ ውንጀላ ፍፁም ከእውነት የራቀ ነው። Link to: ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁን በተመለከተ በትግራይ ተፈናቃዮች የተደረገው መሰረተ ቢስ ውንጀላ ፍፁም ከእውነት የራቀ ነው። ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁን በተመለከተ በትግራይ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top