በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በሰበታ ገላን ጉዳና ፉሪ የዓለም ገና ደብረ ቀርሜሎስ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ተባረከ

ሚያዝያ 22 ቀን 2018 ዓ.ም
በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በሰበታ ገላን ጉዳና ፉሪ ክፍላተ ከተማ ቤተክህነት የዓለም ገና ደብረ ቀርሜሎስ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ሕንጻ ቤተክርስቲያን ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ ፣ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፣ የራያና አከባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ የሲዳማ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳሰ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የቅድስት ሀገር የኢየሩሳሌም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአከ ሰላም ዓለማየሁ ሺፈራው የሸገር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አሥኪያጅ፣ መልአከ ኃይል አባ አፈወርቅ ዮሐንስ የ3ቱም ክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አሥኪያጅ፣ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣የሰንበት ትምሕርት ቤት ዘማሪያን እና ዘማሪያት፣ በርካታ ምዕመናንና ምዕመናት በተገኙበት በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተባርከዋል።
ይህ ታላቅ ቤተ መቅደስ በኪነ ሕንጻ አሰራር በአይነቱ በውበቱ ዘመን ተሻጋሪ መሆኑን ቤተ መቅደስ ሲሆን ግንባታ በተጀነርፕ በ13ኛ ዓመት ተጠናቆ ላዛሬው ለምእቃት ቀ. በቅቷል ።
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ይህ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ተሠርቶ ይጠነቀቃል ተብሎ ባይታሰብም በእግዚአብሔር መልካም ፍቃድ እና በእናንተ ብርታት ለምርቃት በመብቃቱ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል።
ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ በበኩላቸው ይሄንን የደከማችሁበትን ሕንጻ ቤተክርስቲያን ለምርቃት በቅቶ ስላያችሁ እንኳን ደስ አላችሁ ካሉ በኋላ በቤተክርስቲያን የምንሰበሰበብ ለዘለዓለማዊ ድኅነት ነው፤ ቤተክርስቲያን መማጸኛ እንዲሁም የሰውና የቅዱሳን መገናኛ ናትም ብለዋል ስለዚህ ወደ ቤተክርስቲያን የምንመጣው ምድራዊው በረከት፣ ሰማያዊ ክብር ለማግኘት ነውና ቤተክርስቲያን ልንጠብቃት፣ ልንከባከባት ያስፈልጋል በማለት አባታዊ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በተጨማሪም በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ አመራር ሰጪነት ብዙ ልማቶች እየተሠሩ እንደሆነም ጠቅሰዋል፤ ብፁዕነታቸው አክለውም እግዚአብሔር ህዝቡን የሚያገለግል፣ ቤተክርስቲያንን የሚያንጽ አባት ስለተሰጣችሁ እግዚአብሔርን ልታመሰግኑ ይገባልም በማለት ቃለ ቡራኬያቸውን አስተላልፈዋል።
በተመሳሳይ ሁኔታ ለሕንጻ ቤተክርስቲያኑ መሠራት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረጉት ስጦታ ተበርክቶላቸዋል።
በተጨማሪም ደብሩ ለሚያከናውናቸው መሠረታዊ የልማት ሁለገብ G-1 ሕንጻ የመሠረት ድንጋይ አኑረዋል ።
በመጨራሻም በብፁዓን አባቶች ቃለምዕዳንና ቡራኬ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።©ም/ዙ/መ/ገ/ሚዲያ