ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ እና ብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ በኬንያ ናይሮቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲን ጎበኙ

ሚያዚያ 11ቀን2018ዓ.ም
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሚያዝያ 10 ቀን 2018 ዓ.ም በናይሮቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጉብኝት አደረጉ።
በጉብኝቱ ወቅት የሚሲዮኑ ዲፕሎማቶች እና ሠራተኞች ለብፁዓን አባቶች አቀባባል ያደረጉ ሲሆን፣ የሚሲዮኑ ምክትል መሪ ክቡር አምባሳደር ደመቀ አጥናፉ ለብፁዓን አባቶች ስለኤምባሲው አመሰራረት እንዲሁም በሁለቱ አገሮች መካከል ስላለው መልካም ግንኙነት እና ትብብር ገለጻ ሰጥተዋል ሲል ኤምባሲው በማኀኅበራዊ ሚዲያ ገጹ አስተታውቋል።