የጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ጥሪ ተላለፈ።

መስከረም ፲ ቀን ፳፻፲፮ ዓ/ም
አዲስ አበባ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በዓመት ሁለት ጊዜ ከሚያደርጋቸው የምልአተ ጉባኤ ስብሰባዎች አንዱ የሆነው የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ መሆኑ ይታወቃል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የዘንድሮው የጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ከጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፲፮ ዓ/ም ጀምሮ እንደሚካሄድ በመግለጽ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና ጳጳሳት ጥቅምት ፲፩ ቀን ፳፻፲፮ ዓ/ም በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ እንዲገኙ መንፈሳዊ ጥሪውን አስተላልፏል።
ከጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ በፊት ባሉት ዕለታት አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ስብሰባ በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ መሪነት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና ጳጳሳት፣ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የመምሪያና የድርጅት ኃላፊዎች፣የአህጉረ ስብከት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሰበካ ጉባኤያት ምክትል ሊቃነ መናብርትና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ተወካዮች በተገኙበት ይከናወናል።