የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የ፵፪ ኛው ዓለምአቀፍ አጠቃላይ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ስኬቶች፤

October 21, 2023

ጥቅምት ፲ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም
****
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
“””””””””””””””””””””

፩ኛ የጉባኤው ርዕሰ መንበር ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የቤተክርስቲያን ችግሮችና መፍትሔዎችን በሚገባ የገለጸ መልዕክት ማስተላለፋቸውና ጉባኤውን ፍጹም በተረጋጋ መልኩ የመሩበት መሆኑ፤

፪ኛ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕርዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጉባኤው በተረጋጋ መልኩ እንዲካሔድ ከአድሎአዊነት በጸዳ መልኩ ነጻና ፍትሐዊ በሆነ የአመራር ጥበብ ግልጽነት በተሞላበት መንፈስ በመምራት የአመራር ጥበብና ችሎታቸውን
ባረጋገጠ መልኩ በመምራት በታሪክ የሚመዘገብ የመሪነት ሚናቸውን ማሳየታቸው፤

፫ኛ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በትዕግሥትና በምልዓት በጉባኤው ላይ በመሳተፍና ገንቢ ዐሳቦችን በመስጠት በሚገባ የተሳተፉበት ጉባኤ መሆኑ፤

፬ኛ መላው የጉባኤ አባላት በምልዐት፣ያለመሰላቸት፣በመረጋጋትና በትዕግሥት መልዕክቶችን በማዳመጥ ፍጹም መንፈሳዊነት በተሞለበት ሁኔታ የተሳተፉበት ጉባኤ መሆኑ፤

፭ኛ በጉባኤው ላይ የቀረቡ አብዛኛው ሪፖሮቶች ያልተጋነኑ፣በሐቅ ላይ የተመሠረቱ፣ችግሮችና መፍትሔዎች የተጠቆሙባቸው፣ከቅድስት ቤተክርስቲያን የወጡና ወደ ቅድስት ቤተክርስቲያን የመጡ ምእመናን ቁጥር በንጽጽር የተገለጸበት፣የወደፊት አቅጣጫዎች የተጠቆሙበት ሪፖርት የተሰማበት መሆኑ፤

፮ኛ በምልዓት በተደረገው ውይይት ከመሞጋገስና ችግሮችን ከመሸፋፈን ይልቅ ችግሮች በግልጽ የተጠቆሙበት፣ለተገለጹ ችግሮች መፍትሔ ይሆናሉ ተብለው የሚታመንባቸው የመፍትሔ ዐሳቦች የተጠቆሙበት ግልጽና ነጻ ውይይት መደረጉ፤

፯ኛ በቡድን ውይይት ወቅት ለመወያያነጥቦች ተብለው የተለዩ የውይይት ርእሶችን መሠረት ያደረገ ግልጽና ነጻ ውይይቶችን ሳታፊዎች ማድረግ መቻላቸውና ከጉባኤው ተሳታፊዎች በውይይት የተገኙ የመፍትሔ ዐሳቦችና አቅጣጫዎችን በግልጽነት መቀመጣቸው፤

፰ኛ የመወያያ ርእሶችን እንዲያዘጋጁ የተመረጡት ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን አሁናዊ የቤተክርስቲያን ሁኔታን በአግባቡ የሚፈትሹ የመወያያ ርእሶችን በመለየት ቤተክርስቲያን ከፈተና የምትወጣበትን አቅጣጫ የሚያሳዩ ነጥቦችን ማቅረብ መቻላቸው፤

፱ኛ የቡድን ውይይቶቹን እንዲመሩ የተመደቡት የቡድን አወያዮች በቀረበው የመወያያ ርእስ ዙሪያ የቡድን ተወያዮቹ ግልጽነት የተሞላበት ነጻ ውይይት እንዲያደርጉ ማድረጋቸውና በየ ቡድኑ የተነሡ ዐሳቦችን በሚገባ ቀምረው ለምልዓተ ጉባኤው ማቅረባቸው፤
፲ኛ በቡድን ውይይቶቹ የተነሡ ነጻና ግልጽ ዐሳቦችን በጥልቀት በመዘርዘር ተገቢ፣ወቅታዊ፣ግልጽና ተቋማዊ ማጠቃለያን በመስጠት የጉባኤተኛውን ሙሉ ድጋፍ ያገኘና ቀጣይ የሥራ መመሪያ ሆኖ ሊያገለግል የሚችል ማጠቃለያ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕርዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መስጠታቸው፤

፲፩ኛ የጉባኤውን ቆይታ፣የተነሱ፣ዐሳቦችን፣የተቀመጡ የመፍትሔ ዐሳቦችን፣ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በሚገባ በመዘገብ ግልጽና ውጤታማ የዐቋም መግለጫ መቅረቡ በመጨረሻም በተቀመጠው የሽልማት መስፈርት መሰረት ሽልማት ለሚገባቸው ሽልማት መሰጠቱ፤

፲፪ኛ ለተሸላሚዎች የተሰጠው ሽልማት ቤተክርስቲያንን ማዕከል ያደረገ የሁል ጊዜ ማስታወሻ እንዲሆን መደረጉ ወዘተ …. በ፵፪ኛው ዓለም አቀፍ አጠቃላይ ጉባኤ ከተመዘገቡ በርካታ ስኬቶች ጥቂቶቹ ሆነው በታሪክ ተመዝግቧል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • የድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ያስገኘባው ባለ ሦስት ወለል ሁለገብ ሕንጻ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጸሎተ ቡራኬ በዛሬው ዕለት ተመረቋል።
  • የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን ዕድሳት ተጠናቆ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው ተባረከ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ ወደ ቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተጓዘ።
  • አሐዱ ባንክ ላደረገው ሁለተናዊ እገዛ በቋሚ ሲኖዶስ የእውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበረከተለት።
  • የመቱ ፈለገ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያውን ዙር እጩ መምህራን በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመረቀ

Archives

  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የ፵፪ ኛው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የተለያዩ የአቋም መግለጫ ነጥቦችን በማውጣት ተጠናቋል። Link to: የ፵፪ ኛው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ የተለያዩ የአቋም መግለጫ ነጥቦችን በማውጣት ተጠናቋል። የ፵፪ ኛው አጠቃላይ ዓለም አቀፍ የሰበካ መንፈሳዊ... Link to: መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርከ Link to: መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርከ መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርከ
Scroll to top Scroll to top Scroll to top