እግዚአብሔር አምላክ አገራችን ኢትዮጵያን ይጠብቅልን።

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
“ወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምሕረትከ፧ ወይጸግቡ ጠላተ ገዳሞ፤ በቸርነትህ ዓመትን ታቀዳጃለህ፥ ምድረ በዳውም ስብን ይጠግባል።”መዝ. ፷፬÷፲፩

ቸርነትና ምሕረት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነለት አምላካችን አግዚአበሔር ወሰን በሌለው አባታዊ ፍቅሩና መግቦቱ ሳይለየን ጠብቆና አቆይቶ እንኳን ከዘመነ ዮሐንስ ወደ ዘመነ ማቴዎስ ከ፳፻፲፮ ዓ.ም ወደ ፳፻፲፯ ዓ.ም በሰላምና በጤና አሸጋገረን
አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የአንድነት፣ የሥራ፣ የመግባባትና የፍቅር ዓመት ይሁንልን።

እግዚአብሔር አምላክ አገራችን ኢትዮጵያን ይጠብቅልን።
አባ ዲዮስቆሮስ
የደቡብና የደቡብ ምሥራቅ ትግራይ አህጉረ ስብከ፣የቤተ መጻሕፍት ወመዘክርና የማኅበራት ማደራጃ መምሪያ ሊቀ ጳጳስ