የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፲፪ኛ በዓለ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት ተከብሮ ዋለ።

March 3, 2025

የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፲፪ኛ በዓለ ሢመት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት ተከብሮ ዋለ።
************
የካቲት ፳፬ ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም
********
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
+++++++++++++

የቅዱስ ፓትርያርኩ በዓለ ሢመት ላይ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣የጠቅላይ ቤተክህነት መምሪያ ኃላፊዎች፣አምባሳደሮች የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ፣ምዕመናንና ምዕመናት ተገኝተዋል ።

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ በዚሁ ጊዜ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት”ሁላችንም ውሉደ ክህነት በውል ልንገነዘበው የሚገባ ዓቢይ ቁም ነገር፣ ኣሁን ባለን ቁመና ቤተ ክርስቲያንን በሚፈለገው ደረጃ ወደ ቀጣዩ ትውልድ በአስተማማኝ ሁኔታ ማሸጋገር ያዳግታል፤ካሉ በኋላ ላለንበት ዘመን የማይመጥኑ ብዙ የስራ ኣፈጻጸሞች አሉብን፤ እነዚህን ከምር ኣውቀን በማስተካከል ወደ ተሻለ የስራ አፈጻጸም ካልተሻገርን በምድርም፣ በሰማይም፣ በታሪክም፣ በኅሊናም ተወቃሽ ከመሆን ኣናመልጥም፤በማለት ዘመኑን የሚመጥን ሥራ መስራት እንደሚገባ አበክረው ገልጸዋል።

ቅዱስነታቸው በበዓለ ሢመቱ አከባበር ወቅት ያስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል፦

ከሁሉ በፊት ለመላው ውሉደ ክህነትና ሕዝበ ክርስቲያን እግዚአብሔር እንኳን ለዐሥራ ሁለተኛው ዓመት በዓለ ሢመተ ክህነት አደረሳችሁ እንላለን፤

“አአኵተከ አባ አግዚአ ሰማያት ወምድር አስመ ኃባስኮ በዝንቱ አምጠቢባን ወስማትምራ ወከሠትኮ ሰሕፃናት አወ አባ አስመ ከማሁ ኮነ ሥምረትከ በቅድሜከ፤ የሰማይና የምድር ጌታ ኣባት ሆይ! ይህጓጓ ከጥበበኞችና ከአስተዋዮች ሰውረህ ሰሕዓናት ስሰ ገስጥህሳቸው ኣመሰግንሃለሁ፤ ኣዎን አባት ሆይ! ፈቃድህ በፊትህ አንዲህ ሆኖኣልና”(ማቴ.፲፩÷፳፭-፳፮)

የጌታችን ዐኔመኝነትይህ የጌታችን የአምላካችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስክርስቶስ ትምህርተ ወንጌል ነው፤ ጌታችን በዚህ ኣስተ ምህሮው የሰማዩና የምድሩ ጌታና አባት ፈቃድ ምን እንደሆነ በግልጽ አስቀምጦልናል፤

ይኸውም የእግዚአብሔር ፈቃድ፣ የመንግሥተ እግዚአብሔርን ምሥጢር ማለትም ኢየሱስ ክርስቶስን የማወቅ ዕድል፣ እናውቃለን እንራቀቃለን ከሚሉ ጥበበኞችና አስተዋዮች መሰወር፤ በአንጻሩ ደግሞ እንደ ሕፃናት የዋሃንና ንጹሓን ለሆኑ ምእመናን መግለጽ እንደሆነ ነው፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ የማይናወጥ ፈቃድ ነው፤ትልቁ የእግዚአብሔር ጥበብና ምስጢር ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንደሆነ ቅዱስ መጽሐፍ ኣበክሮ ይነግረናል፤እግዚብሔር አምላካችን ዓለም ይህንን ምስጢርና ጥበብ ኣውቆ አምኖና ተቀብሎ መጻኢ ዕድሉን እንዲያሳምር ይጐተጕታል፤ ጌታችን በአካለ ሥጋ በዚህ ዓለም ተገልጾ በሚያስተምርበት ጊዜ ይህ ጥበብና ምስጢር የተሰወረባቸው የማኅበረ ሰብ ክፍሎች ነበሩ፤ ምስጢሩ ሊሰወርባቸው የቻለው በጥበባቸውና በዕውቀታቸው የመመካት ችግር ስለነበራቸው እንደሆነ ቃሉ ይጠቁማል መቼም እኛ ሰዎች በሥልጣን፣ ወይም በዕውቀት ወይም ደግሞ በሀብት በአጠገባችን ካሉ ሰዎች የተሻልን፤ነን ብለን ስናስብ የትዕቢት መንፈስ ይወረናል፤ ትዕቢት ደግሞ እውነትንና ዓቅማችንን እንዳናውቅ ኣእምሮኣችንንበመሽበብ ለሰዎች ሓሳብና ሰብእና አክብሮት እንዳንሰጥእንደሚያደርገን የታወቀ ነው፤

በወቅቱ ጠቢባንና አስተዋዮች ነን የሚሉ የአይሁድ አለቆችና መሪዎችም በዚህ ደካማ ሰብኣዊ ጠባያቸው በራሳቸው ዕውቀት ስለተማመኑ የእግዚብሔር ጥበብናጎን ምሥጢር የሆነውን ክርስቶስን ለማወቅና ለመቀበል ዝንባሌውና ፍላጎት ኣልነበ ራቸውም፤ፍላጎት ኣልነበራቸውም፤ በመሆኑም ፍላጎት ላለው ጨምሮ መስጠት ለሌለው ግን ያለውንም መንሣት ጠባዩ የሆነ እግዚአብሔር አምላክየነበራቸውንም ጨርሶሰውሮባቸዋል፤ ምክንያቱም የእግዚአብሔር ፈቃድ ምስጢሩን ከትዕቢተኞች መሰወር ለትሑታን ግን መግለጽ በመሆኑ ነው፤

በጌታችን ኣስተምህሮ እዚህ ላይ ሕፃናት እየተባሉ ያሉ የእሱን መሲሕነት አውቀው ኣምነውና ተቀብለው ከእርሱ ጋር ይጓዙ የነበሩ አይሁዳውያን ተከታዮቹን ነው፤ እነሱ በቅንነትና በትሕትና እንዲሁም የዕውቀት ሕፃናት እንደሆኑ አውቀው የበለጠ ዕውቀትን ከሱ ለማግኘት ፍላጎት ስለነበራቸው እሱነቱን ገለጸላቸው፤
ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ጥንትም ሆነ ዛሬ የነበረ ያለና የማይለወጥ ቀዋሚ ፈቃዱ ነው፤ ከዚህ አንጻር ዛሬም ቢሆን ጥበቡን ከትዕቢተኞች ይሰውራል ለሕፃናት አማንያን ግን ይገልጻል፤

ዛሬም እንደቀድሞው ዓለም በዕውቀቷ በሥልጣንዋና በሀብቷ እየተመካች ለእግዚአብሔር ቃል ጆሮ ዳባ ልበስ ስላለች ምስጢሩና ጥበቡ ተሰውሮባታል፤ከክርስቶስ ጥበብነትና ምስጢርነት ይልቅ ምርጫዋ የጨለማው ገዥ ጠባያትን መቀበልና ማስፋፋት ምርጫዋ ሆኖአል፤

ለዚህም ተግባርዋ የተመሳሳይ ፆታ ነውረ ኃጢኣትና የአምልኮ ባዕድ እምነቶች ሕጋዊ ዕውቅና እንዲያገኙ የምታደርጋቸው ጥረቶችንና ለኔ ለኔ በሚል የስግብግብ አመለካከት የምታካ
ሂዳቸው ኣውዳሚ ጦርነቶች ዋና ዋና ማሳያዎች ሆነው ይገኛሉ፣ የሰው ልጅም ከነዚህ እኩያት ተግባራት በነፍሱ ብቻ ሳይሆን በሥጋዊ ኑሮውም ቢሆን ከጉዳት በቀር ቅንጣት ታህል ጥቅም ማግኘት እንደማይችል ማወቅ ተስኖታል፣ እግዚአብሔር ግን የዚህ ዓለም ጥበብ ሞኝነት እንደሆነ አጠንክሮ ነግሮናል፣ ታድያ የዓለም ጥበብና ዕውቀት በእግዚአብሔር ፊት ይህን ያህል ሞኝነት ከሆነ እኛ ሕፃናት ኣማንያን ምን እየሰራን ነው? የሚለው ተስእሎት የዚህ ዕለት ኣንኳር ጥያቄአችን ሊሆን ይገባል፤

ከሁሉ በፊት እግዚብሔር ይህንን የክርስቶስን ምስጢርነት የገለጸልን ሕፃናት ሆነን በመገኘታችን እንደሆነ ከእርሱ የበለጠ መስካሪ ኣያስፈልገንምና እሱን ኣጥብቀን እንጨብጥ፣ ቀጥሎም በዚህ ቅዱስ ፈቃዱ ሕፃናት የሆነው እኛን በልዩ ምርጫው ፓትርያርክ፣ ሊቀ ጳጳስ ፣ኤጲስ ቆጶስ፣ ቀሲስ፣ዲያቆን፣ ምእመንና ማእምንት በሚል ሰይሞ በመንግሥቱ ውስጥ እንድናገለግል የተቀበለን መሆኑን ለአፍታ እንኳ አንዘንጋ፤በጎቹን በንጽህና እና በቅድስና እንድንጠብቅ፣ በምድር ላይ ሰላምና ሰላም ብቻ እንድናውጅ፣ ፍትሕ ርትዕ እንዳይዛባ እንድንመክር፣ ኣንድነትና እኩልነት እንዳንነጣጥል፣ ፍቅርና ይቅርታ እንዳይቀዘቅዝ ሌት ተቀን እንድናስተምር የሰላም ወንጌልን አስጨብጦናል፤ ከሁሉ በላይ ደግሞ በቤቱ ቤተኛ ሆነን እንድናዝና እንድናዝዝ ኣድርጎናል፤ ታድያ በቤቱ ሆነን የምንሰጠው አገልግሎት ለባለቤቱ የሚመጥን እንዲሆን ያስፈልጋል፤ ተገልጋዮች ምእመናንም በአገልግሎታችን ደስተኞች መሆናቸውን ማረጋገጥ ኣለብን፤

ሁላችንም ውሉደ ክህነት በውል ልንገነዘበው የሚገባ ዓቢይ ቁም ነገር፣ ኣሁን ባለን ቁመና ቤተ ክርስቲያንን በሚፈለገው ደረጃ ወደ ቀጣዩ ትውልድ በአስተማማኝ ሁኔታ ማሸጋገር ያዳግታል፤ ላለንበት ዘመን የማይመጥኑ ብዙ የስራ ኣፈጻጸሞች አሉብን፤ እነዚህን ከምር ኣውቀን በማስተካከል ወደ ተሻለ የስራ አፈጻጸም ካልተሻገርን በምድርም፣ በሰማይም፣ በታሪክም፣ በኅሊናም ተወቃሽ ከመሆን ኣናመልጥም፤

ከላይ ጀምሮ እስከታች ያለው ውሉደ ክህነት ከዚያም መላው ሕዝበ ክርስቲያን በዚህ ላይ የበኩሉን ኃላፊነት ለመወጣት በርትቶ እንዲሰራ ያስፈልጋል፤

ሌላው እኛ የሃይማኖት አገልጋዮች ሃይማኖትን ስንጠብቅ ሕዝብን ይዘን ነው፤ ያለ ሕዝብ ሃይማኖት ይኖራል ተብሎ አይታሰብም፤ የሕዝብም መኖር ያለሰላም አይታሰብም፤ ሃይማኖት እንዲኖር ሕዝብ መኖር አለበት፤ሕዝብ እንዲኖር ሰላም መኖር አለበት፣ እነዚህ የማይነጣጠሉ ናቸው፤ አሁን ባለንበት ጊዜ ግን ፈተናቸው
በዝቶአል፤ ስለሆነም በሕዝቦች አንድነትና ሰላም በፍትሕና እኩልነት ላይ አጥብቀን እንድናስተምር የወቅቱ ኣባታዊ ጥሪያችንና መልእክታችን ነው፤

እግዚአብሔር መልካም በዓለ ሢመተ ክህነት ያድርግልን!

“እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ”
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርአሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ
ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
የካቲት ፳፬ ቀን ፳፻፲ወ፯ ዓ.ም.
ኣደስ አበባ አቶዮጵያ

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና ጊዜያዊ ርዳታም አበረከተ።
  • “በአርሲ የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንሠራለን” የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች
  • ብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅ በሀገረ ስብከቱ ለካህናት የሚሰጠውን ሥልጠና በጸሎትና በቡራኬ አስጀመሩ።
  • ቋሚ ሲኖዶስ በምሥራቅ አርሲ ተገኝተው የተጎዱ ወገኖችን የሚያጽናኑ በፁዐን አባቶችን መደበ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን የልዑካን ቡድን ከኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ሰላም ሚኒስቴርና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ተወያየ።

Archives

  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ትምህርተ ሃይማኖትን የያዘ መጽሐፍ በእንግሊዝኛ ቋንቋ በአሜሪካ ታትሞ ተመረቀ፤ በሀገር ውስጥ ለሚገኙ አንባብያን በቅርቡ በኢትዮጵያ እንደሚታተም ተገለጸ። Link to: ትምህርተ ሃይማኖትን የያዘ መጽሐፍ በእንግሊዝኛ ቋንቋ በአሜሪካ ታትሞ ተመረቀ፤ በሀገር ውስጥ ለሚገኙ አንባብያን በቅርቡ በኢትዮጵያ እንደሚታተም ተገለጸ። ትምህርተ ሃይማኖትን የያዘ መጽሐፍ በእንግሊዝኛ... Link to: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አዲሱን የጀርመን አምባሳደር በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡ Link to: ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አዲሱን የጀርመን አምባሳደር በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋገሩ፡፡ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top