በሸገር ሀገረ ስብከት የኮዬ ገላን ክፍለ ከተማ ደንጎራ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ሕንጻ የቤተክርስቲያን በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ቡራኬ ቅዳሴ ቤቱ ከበረ

ሚያዚያ 24 ቀን 2018 ዓ.ም
ሚያዝያ 24 ቀን 2018 ዓም በተካሄደው የሕንጻ ቤተክርስቲያን ምርቃት ሥነ ሥርዐት ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንደተናገሩት “እንኳን ደስ አላችሁ፣ ስትደክሙበት ለነበረው ሥራችሁ ለፍጻሜ በቅቷል።” ብለዋል። ብፁዕነታቸው አክለውም “የድካማችሁን ፍሬና የሥራችንን ውጤት ለማየት ያበቃን አምላካችን እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይድረሰው።” ሲሉ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
ብፁዕ አቡነ ሚካኤል የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሉቀ ጳጳስ ባስተላለፉት መልእክት ቤተክርስቲያን የሚሠራ የተፈቀደለት ነው። እናንተ ተፈቅዶላችሁ ቤተክርስቲያን ስለ ሠራችሁ እንኳን ደስ አላችሁ። ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ በርናባስ የዋግህምራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአከ ኃይል አባ አፈወርቅ ዮሐንስ የመልካ ኖኖ፣ጉጂ ገፈርሳ ክፍለ ከተማ ኃላፊ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የለሚ ኩራ ሥራ አስኪያጅ፣ ሊቀ ልሣናት በዳሳ ቶላ የክፍለ ከተማው ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የአጥቢያው ምእመናንና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።©Eotc tv.