ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ ሥልጠና በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከትናት በተሻለ መልኩ ለመሥራት በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን ገለጹ
መጋቢት ፲፯ / ፳፻፲ወ፰ ዓ.ም
ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አቡነ ሳዊሮስ ሥልጠና በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከትናት በተሻለ መልኩ ለመሥራት በእጅጉ አስፈላጊ መሆኑን ገለጹ።
ብፁዕነታቸው ይህንን የይህንን ያሉት በዛሬው ዕለት የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት የስብከተ ወንጌል ክፍልና የሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ ክፍል በጋራ ባዘጋጁት የአንድ ቀን ሥልጠና ላይ ነው።
በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ለሠልጣኞች አባታዊ መመሪያና ቡራኬ ሰጥተዋል።
ብፁዕነታቸው ሥልጠና በቤተ ክርስቲያንናችን አገልገሎት ውስጥ ከትናት የተሻለ ለመሥራት በእጅጉ እንደሚያስፈልግ አሳስበው በቀጣይም እንዲህ ዓይነቶች መርሐ ግብራት እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
አክለውም ሀገረ ስብከቱ ከባለፈው ዓመት በበለጠ መልኩ የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ በመፈጸም አርአያነት ባለው መልኩ ጥሩ የአገልግሎት አፈጻጸም እንዲኖረው አሳስበዋል።
በዕለቱ በመምህራነ ወንጌል አማካኝነት የቀረቡት ሦስት ዋና ዋና የሥልጠና ርዕሶች በቤተክርስቲያናችን አስተምህሮ ላይ ተመሥርተው በዕቅበተ ዕምነት ፣ መልኩ ጥልቅ ትንተና ተሰጥቶባቸዋል፦
💠ዕቅበተ እምነት (Apologetics) በላዕከ ወንጌል መምህር ለሜሳ ሚልኬሳ፤
💠ወጣትነትና መንፈሳዊነት በመጋቤ ወንጌል ሄኖክ ታዬ ፤
💠በሐዋርያዊት ቤተክርስቲያን፤ ሐዋርያዊ ተልዕኮአችን በዘመናችን በመጋቤ አእላፍ ተስፋዬ ቂጤሳ ጥናታዊ መነሻ ትምህርታዊ ጽሐፎች ቀርበዋል።
በቀረቡት ጽሑፎች ላይ ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን ከተሳታፊዎቹ ጥያቄና አስተያያት ቀርቦባቸው ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ መልአክ ሰላም ቀሲስ ዓለማየሁ ተፈራ የሸገር ሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ ፣መጋቤ አእላፍ ተስፋዬ ቂጤሳ የስብከተ ወንጌል ዋና ሐላፊ ፣ መጋቢ ወንጌል ሄኖክ ታዬ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ሐላፊ፣ የክፍለ ከተማ ሥራ አስኪያጆች ፣ የክፍለ ከተማ የስብከተ ወንጌል ክፍል ሐላፊዎች፣ የገዳማትና አድባራት ሰባክያንና የሰንበት ትምህርት ቤቶች አመራሮች በሥልጠናው ተሳትፈዋል።
©የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ አገልግሎት