የ፳፻ ፲ወ፰ ዓ/ም የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የጸሎት መርሐ ግብር በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተከናወነ

ሚያዚያ ፳፯ ቀን ፳፻፲ወ፰ ዓ/ም
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የ፳፻ ፲ወ፰ ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የመክፈቻ ጸሎት መርሐ ግብር በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ተከናወነ።
በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በተከናወነው የጸሎት ሥነ-ሥርዓት ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያውና የድርጅቶቹ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
የግንቦት ፳፻ ፲ወ፰ ዓ/ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ምልዓተ ጉባኤ በቋሚ ሲኖዶስ ተዘጋጅተው በአጀንዳ አሪቃቂ ኮሚቴ ታይተውና በምልዓተ ጉባኤ ተመርምረው በሚጸድቁ አጀንዳዎች ዙሪያ በጥልቀት በመወያየት ልዩ ልዩ ውሳኔዎችን ያስተላልፋል።