የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

በቡራዩ ከተማ የተገነባው “ፈለገ ጥበብ (ቡርቃ ኡጉማ)” አፀደ ሕፃናት ትምህርት ቤት ተመረቀ።

July 19, 2026
በቡራዩ፣ ገፈርሳ ጉጄ እና መልካ ኖኖ ክፍላተ ከተማ በሚገኙ ገዳማትና አድባራት ሙሉ ወጪ የተገነባውና “ፈለገ ጥበብ (ቡርቃ ኡጉማ)” የተሰኘው አፀደ ሕፃናት ትምህርት ቤት በይፋ ተመርቋል ።
በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ
አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ተገኝተው ትምህርት ቤቱን መርቀዋል።
በተጨማሪም የሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሰላም ዓለማየሁ ተፈራ፣ የቡራዩ ገፈርሳ ጉጄ እና መልካ ኖኖ ክፍላተ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ኃይል አባ አፈወርቅ ዮሐንስ፣ የቡራዩ ክፍለ ከተማ ዋና አስተዳዳሪ
አቶ ዓሥራት አባተ እንዲሁም ሌሎች የሸገር ከተማ እና የቡራዩ ክፍለ ከተማ የመንግሥትና የቤተ ክርስቲያን የሥራ ኃላፊዎች፣
አገልጋዮችና ምዕመናን በምረቃው ላይ ተገኝተዋል።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ በቀረበው ሪፖርት መሠረት፣ የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች፣ የሰበካ ጉባኤ አባላትና የተለያዩ የሥራ
ኃላፊዎች የገቡትን የገንዘብ ቃል ኪዳን ከሠራተኞችና ከምዕመናን ጋር በመተባበር ገቢ በማድረጋቸው ግንባታው በተሳካ ሁኔታ
ሊጠናቀቅ ችሏል። የከታ ወረዳ ነዋሪዎችና የትምህርት ማኅበረሰቡም ትምህርት ቤቱ ለአገር ተረካቢ ትውልድ መፍለቂያ ምንጭ እንደሚሆን እምነታቸውን ገልጸዋል።
ይህ አፀደ ሕፃናት ትምህርት ቤት የተገነባበት ዋነኛ ዓላማ በአገራችን የመንግሥት ዘመናዊ ትምህርት የሚጀምረው ከአንደኛ (1ኛ)
ክፍል በመሆኑና ቅድመ መደበኛ (መዋዕለ ሕፃናት) ትምህርት በከፍተኛ ክፍያ በግል ትምህርት ቤቶች ብቻ ስለሚሰጥ የሚፈጠረውን
የትምህርት ተደራሽነት ልዩነት ለመቅረፍ እንደሆነ ተጠቅሷል። አቅም የሌላቸው ሕፃናት ያለ ቅድመ መደበኛ ዝግጅት አንደኛ (1ኛ)
ክፍል ሲገቡ ከሌሎች ጋር እኩል ለመራመድ የሚገጥማቸውን የአቅም ውስንነት ለመሙላት ትምህርት ቤቱ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው
ተገልጿል።
በምረቃው ወቅት ንግግር ያደረጉት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትምህርትን በየዛፉ ሥርና
በየአድባራቱ የጀመረች፣ ፊደል ቀርጻና ቀለም በጥብጣ በርካታ መጻሕፍትን የጻፈች መሆኗን አስታውሰዋል። ቤተ ክርስቲያን በማኅበራዊ
ሕይወት ውስጥ የምታበረክተውን ሰላም የማውረድ ሥራና ታቦት ይዛ የአገርን ሉዓላዊነት ለማስከበር እስከ ጦር ግንባር ድረስ ያደረገችውን ጉዞም ጠቅሰዋል።
ብፁዕነታቸው አክለውም “ትምህርት ቤት ዜጎች የሚቀረጹበት በመሆኑ ከሁሉ የላቀ ትልቅ ሥራ ነው” ካሉ በኋላ፣ ትምህርት ቤቱ
ሁሉንም በጋራ የሚያገለግልና ለሕዝብ ጥቅም የተሠራ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።
አጠቃላይ ግንባታው በአምስት መቶ ዘጠና ሰባት ነጥብ ስምንት ስድስት (597.86) ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያረፈ ሲሆን፣
እያንዳንዳቸው ከአርባ እስከ አምሳ (40 እስከ 50) ተማሪዎችን ማስተናገድ የሚችሉ ክፍሎችን ይዟል። ትምህርት ቤቱ በአጠቃላይ አሥራ ስድስት (16) ክፍሎችን የያዘ ሲሆን፣ የሚከተሉትን ዝርዝሮች ያጠቃልላል።
1. ስምንት (😎 መማሪያ ክፍሎች
2. አንድ (1) የርዕሰ መምህር አስተዳደር ቢሮ
3. አንድ (1) የተማሪዎች መመገቢያ ክፍል
4. ሁለት (2) የሕፃናት ተማሪዎች ማረፊያ (መኝታ) ክፍሎች
5. አንድ (1) የጽዳት ዕቃ ማስቀመጫና ልብስ መቀየሪያ ክፍል
6. አንድ (1) የመምህራን ማረፊያና ጋዎን መቀየሪያ ክፍል
7. ሁለት (2) የመምህራን መጸዳጃ ክፍሎች በተጨማሪም አምስት በአምስት (5 በ 5) ሜትር የሆነ የመጸዳጃ ሴፍቲ ታንከር፣ ባለ ስድስት (6) ክፍል የተማሪዎች መጸዳጃ
ቤት፣ በሰማንያ (80) ቆርቆሮ የተሠራ የተማሪዎች ምግብ ማብሰያ ክፍልና ባለ አንድ (1) ክፍል የጥበቃ መኖሪያ ቤት ተገንብቶለታል።
ለግንባታው በጥሬ ገንዘብና በማቴሪያል በድምሩ ስድስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሰማንያ ስድስት ሺህ ሦስት መቶ አሥራ ስድስት ብር
ከሃምሳ ሳንቲም (6,586,316.50) የተገኘ ሲሆን፣ ለግንባታው ሥራ አምስት ሚሊዮን አምስት መቶ ሰላሳ ሰባት ሺህ አሥራ ሰባት ብር ከሃምሳ ሁለት ሳንቲም (5,537,017.52) ወጪ ተደርጓል።
በሥነ ሥርዓቱ ማጠቃለያ ላይ የትምህርት ቤቱ ቁልፍ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ አማካኝነት ለቡራዩ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ለአቶ ፀጋዬ አመና የተላለፈ ሲሆን፤ ቤተ ክርስቲያንን የሚገልጽ ስያሜ ይሰጠው በሚለው ጥያቄ መሠረት፣ ቀደም ሲል “ቡኡራ ቦሩ” ተብሎ ይጠራ የነበረው ይህ ትምህርት ቤት በብፁዕነታቸው “ፈለገ ጥበብ አፀደ ሕፃናት (ቡርቃ ኡጉማ)” ተብሎ ተሰይሟል።
©Eotc tv
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr000043.jpeg 299 448 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-07-19 14:52:062026-07-19 14:52:06በቡራዩ ከተማ የተገነባው “ፈለገ ጥበብ (ቡርቃ ኡጉማ)” አፀደ ሕፃናት ትምህርት ቤት ተመረቀ።
Search Search

Recent Posts

  • የድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ያስገኘባው ባለ ሦስት ወለል ሁለገብ ሕንጻ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጸሎተ ቡራኬ በዛሬው ዕለት ተመረቋል።
  • የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን ዕድሳት ተጠናቆ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው ተባረከ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ ወደ ቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተጓዘ።
  • አሐዱ ባንክ ላደረገው ሁለተናዊ እገዛ በቋሚ ሲኖዶስ የእውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበረከተለት።
  • የመቱ ፈለገ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያውን ዙር እጩ መምህራን በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመረቀ

Archives

  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የቅድስት ልደታ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በዲግሪ መርሐ ግብር እና በቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና ያስተማሯቸውን ተማሪዎች አስመረቀ። Link to: የቅድስት ልደታ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በዲግሪ መርሐ ግብር እና በቴክኒክ እና ሙያ ሥልጠና ያስተማሯቸውን ተማሪዎች አስመረቀ። የቅድስት ልደታ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በዲግሪ መርሐ... Link to: የሀገር አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች ሥልጠና በወንጪ ሐይቅ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ታሪካዊ ጉብኝት በማድረግ ተጠናቀቀ። Link to: የሀገር አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች ሥልጠና በወንጪ ሐይቅ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ታሪካዊ ጉብኝት በማድረግ ተጠናቀቀ። የሀገር አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች ሥልጠና...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top