የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የሀገር አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች ሥልጠና በወንጪ ሐይቅ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ታሪካዊ ጉብኝት በማድረግ ተጠናቀቀ።

July 19, 2026
ሐምሌ ፲፩ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም.
ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
“የሕዝብ ግንኙነት ስኬት ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት” በሚል መሪ ቃል ለሀገር አቀፍ የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በከፍተኛ ዝግጅት ሲሰጥ የሰነበተው ፫ኛው ዙር ሥልጠና በዛሬው ዕለት በወንጪ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ጉብኝት ተጠናቋል።
የዚሁ ታሪካዊ ሥልጠና ማጠቃለያ ይሆን ዘንድ የአህጉረ ስብከት የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በወንጪ ወረዳ በሚገኘው ታዋቂው የወንጪ ሐይቅ ቅዱስ ቂርቆስ አንድነት ገዳም ልዩ የጉብኝት መርሐ ግብር ተከናውኗል።
ይህ ታላቅ የጉብኝት እና የመስክ ውይይት መርሐ ግብር በወንጪ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ሊከናወን የቻለበት ምክንያት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ሀገረ ስብከት በመሆኑና መርሐ ግብሩን በዚህ ታሪካዊ ሥፍራ ቢከናወን የሥልጠናውን ማጠቃለያ ይበልጥ ልዩና ታሪካዊ መርሐ ግብር ስለሚደርገው በልዩ ሁኔታ መመረጡ ተገልጧል።
ሠልጣኞቹ በጉብኝቱ ወቅት የወንጪ ሐይቅ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም በ፲፫ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተመሠረተና የታላቅ መንፈሳዊ ታሪክ ባለቤት መሆኑን የተረዱ ሲሆን አካባቢው በገበታ ለትውልድ መርሐ ግብር የቱሪስት መስህብ ሆኖ መሠራቱን ተከትሎ ወደ ሥፍራው ለጉብኝት የሚጓዙ ጎብኚዎች ጥንታዊውን የቅዱስ ቂርቆስ ገዳምን እንዲጎበኙ ለማድረግ ይቻል ዘንድ ጥንታዊ መሠረቱን ሳይለቅ በአዲስ መልክ እንዲሠራ ክቡር የኢፌዲሪ ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ በሰጡት ቀጥተኛ ትዕዛዝ የሚሠራ መሆኑን በጉብኝቱ ወቅት ተገልጿል።
በገዳሙ የሚከናወኑትን የልማት ሥራዎች በርካታ ብፁዓን አባቶች የጎበኙትና ለግንባታ ሥራው አስተዋጽኦ ያበረከቱ ሲሆን በገዳሙ ውስጥ በርካታ አህጉራዊና ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው ታላላቅ የልማት ሥራዎች በመከናወን ላይ እንደሚገኙም የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎቹ ተመልክተዋል።
ሠልጣኞቹ በገዳሙ ባደረጉት ጉብኝት ወቅት የአብነት ትምህርት ቤት ግንባታ፣ የሙዚየም ግንባታ፣ የቤተ መቅደስ ግንባታ፣ የቤተልሔም ሕንጻ እንዲሁም አጠቃላይ የቅጥርና የመሠረተ ልማት ግንባታ ሂደቶች በፍጥነት በመገንባት ላይ መሆናቸውን ተመልክተዋል። በጉብኝቱ ወቅት ስለ ገዳሙ ጥንታዊ አመሠራረት፣ ስለ ነበረው ታሪክና አሁን ስላለው ሁለንተናዊ የዕድሳት ሂደት ሰፊና ጥልቅ ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን፣ ሠልጣኞቹም ካዩት ታላቅ መንፈሳዊ ቅርስና የልማት እንቅሰቃሴ በመነሳት የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታና አበረታች አስተያየት በስፋት ገልጸዋል።
ከዚሁ መንፈሳዊ የጉብኝት መርሐ ግብር ማጠቃለያ በኋላ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ በሊቀ ሥዩማን እስክንድር ገብረ ክርስቶስ አማካኝነት ለሠልጣኞቹ የተሳትፎ የምስክር ወረቀት በታላቅ ሥነ ሥርዓት ተበርክቶላቸዋል።
የመምሪያው ኃላፊ ሊቀ ሥዩማን እስክንድር ለሠልጣኞቹ ባስተላለፉት ጥብቅ መመሪያ፤ ኃላፊዎቹ በሥልጠናው ወቅት ያገኙትን ከፍተኛ ዕውቀትና ክህሎት ወደየአህጉረ ስብከታቸው በሚመለሱበት ወቅት ያለምንም መዘግየት ወደ ተግባር እንዲቀይሩት አሳስበዋል። አያይዘውም ተሳታፊዎቹ የእውነት ጠበቃ በመሆን የቅድስት ቤተ ክርስቲያን እውነተኛ ድምፅ እንዲሆኑ፣ በተመደቡበት የኃላፊነት ቦታና አገልግሎት ሁሉ ሳይታክቱና ሳይሰለቹ በርትተው እንዲሠሩ፣ እንዲሁም ለሃይማኖታቸውና ለቤተ ክርስቲያናቸው በጽናት እንዲቆሙ በብርቱ ቃል አስገንዝበዋል።
በመጨረሻም የመምሪያው ኃላፊ ሊቀ ሥዩማን እስክንድር ገብረ ክርስቶስ ይህ አገር አቀፍ የሥልጠናና የጉብኝት መርሐ ግብር እጅግ የተሳካ፣ ፍሬያማና ውጤታማ ሆኖ ይጠናቀቅ ዘንድ ሙሉ የገንዘብ ወጪውን በመሸፈን የላቀ ክርስቲያናዊ አጋርነቱንና ታሪካዊ ድጋፉን ላሳየው ለአሐዱ ባንክ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም ከፍተኛ ምስጋናቸውንና አድናቆታቸውን አቅርበው መርሐ ግብሩ ተፈጽሟል።
ፎቶ Eotc tv
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr000044.jpeg 299 448 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-07-19 14:55:302026-07-19 14:55:30የሀገር አቀፍ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊዎች ሥልጠና በወንጪ ሐይቅ ቅዱስ ቂርቆስ ገዳም ታሪካዊ ጉብኝት በማድረግ ተጠናቀቀ።
Search Search

Recent Posts

  • የድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ያስገኘባው ባለ ሦስት ወለል ሁለገብ ሕንጻ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጸሎተ ቡራኬ በዛሬው ዕለት ተመረቋል።
  • የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን ዕድሳት ተጠናቆ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው ተባረከ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ ወደ ቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተጓዘ።
  • አሐዱ ባንክ ላደረገው ሁለተናዊ እገዛ በቋሚ ሲኖዶስ የእውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበረከተለት።
  • የመቱ ፈለገ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያውን ዙር እጩ መምህራን በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመረቀ

Archives

  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: በቡራዩ ከተማ የተገነባው “ፈለገ ጥበብ (ቡርቃ ኡጉማ)” አፀደ ሕፃናት ትምህርት ቤት ተመረቀ። Link to: በቡራዩ ከተማ የተገነባው “ፈለገ ጥበብ (ቡርቃ ኡጉማ)” አፀደ ሕፃናት ትምህርት ቤት ተመረቀ። በቡራዩ ከተማ የተገነባው “ፈለገ ጥበብ (ቡርቃ... Link to: ልዩ ምስጋና Link to: ልዩ ምስጋና ልዩ ምስጋና
Scroll to top Scroll to top Scroll to top