የሰማዕቱ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ የ34ኛው ዓመት የፍልሠተ ዓፅም መታሰቢያ በዓል በግል ገንዘባቸው በጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት እየተከበረ ይገኛል።
ሐምሌ 4 ቀን 2018 ዓ.ምሐምሌ 4 የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሁለተኛው ፓትርያርክ አጽማቸው በግፍ ተገድለው ከተቀበረበት ቦታ ከ13 ዓመት በኋላ በእርሳቸው መሪነት ወደታነጸው ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል በክብር ያረፈበት ዕለት ነው።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሁለተኛው ፓትርያርክ የሰማዕቱ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ የ34ኛው ዓመት
የፍልሠተ ዓፅም መታሰቢያ በዓል፣ በአዲስ አበባ በሚገኘው በጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል ብፁዕ አቡነ ማርቆስ የስብከተ ወንጌል እና ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ ሓላፊ ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል የምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ መልአከ ፀሐይ ቆሞስ አባ ኃይለኢየሱስ ተመስገን ጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል አስተዳዳሪ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ አገልጋይ ካህናትና በርካታ ምዕመናን
በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ የቤተ ክርስቲያንን ነፃነት፣ መብትና ቀኖና ለማስጠበቅ ባሳዩት የማይናወጥ ጽናት ምክንያት በወቅቱ
በነበረው የደርግ ሥርዓት በ1968 ዓ.ም ለእስራት ተዳርገው፣ በ1971 ዓ.ም በግፍ ታንቀው ሰማዕትነትን የተቀበሉ ታላቅ የቤተ
ክርስቲያን አባት ናቸው።
የቅዱስነታቸው አስከሬን በወቅቱ በድብቅ ተቀብሮ ከቆየ በኋላ፣ የደርግ ሥርዓት መውደቅን ተከትሎ በ1984 ዓ.ም በክብር ተቆፍሮ ወጥቶ (ፍልሠተ ዓፅም ተደርጎ) በአሁኑ ማረፊያቸው በሆነው በጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓት እንዲያርፍ ተደርጓል።
ይህን ታሪካዊና መንፈሳዊ ኩነት ለመዘከር ዛሬ እየተካሄደ ባለው መርሐ ግብር ላይ፤ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሆኑት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የተገኙበት የጸሎትና የምሥጋና መርሐ ግብር ተከናውኗል። በተጨማሪም የሰማዕቱ ፓትርያርክ ለቤተ
ክርስቲያንና ለሀገር ያበረከቱት ዘርፈ ብዙ መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊና ትምህርታዊ አስተዋፅኦ እንዲሁም ስለ ሃይማኖታቸውና ስለ
መንጋቸው የከፈሉት ታላቅ መሥዋዕትነት በመዘከር ላይ ይገኛል።
የመታሰቢያ በዓሉን ሙሉ ሥነ ሥርዓት፣ የተላለፉትን አባታዊ መልእክቶችና ዝርዝር ዘገባዎችን በቀጣይ ይዘን የምንመለስ ይሆናል።©EOTC t.v