የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የገዳማት መምሪያ ለአህጉረ ስብከትና ገዳማት የሚያገለግሉ ልዩልዩ የቤተ ክርስቲያን መገልገያና የሶላር ኃይል ማመንጫ መሳሪያዎችን አበረከተ።

August 30, 2026
ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ- ኢትዮጵያ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በመንበረ ፓትሪያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት መምሪያ አስተባባሪነት ለተለያዩ አህጉረ ስብከትና ገዳማት አገልግሎት የሚውሉ ልዩልዩ ቁሳቁሶችና የሶላር ኃይል ማመንጫዎች ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ቢብዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ተበረከተ።
ስጦታውን ያበረከቱት የዋሽንግተን ዲሲ፣ ኦሪገንና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ሲሆኑ፣ እሳቸው ከሚያስተዳድሩት ሀገረ ስብከት ምዕመናንና የመንፈስ ወቅዱስ ልጆቻቸውን አስተባብረው በየጊዜው በሚላከው የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፍ በተለይም በገጠራማ የአገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ገዳማትና አድባራት እንዲጠናከሩ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያደረጉ ይገኛሉ።
በዚህም መሠረት ባለፈው ዓመት ለ36 ገዳማት የሶላር ኃይል ማመንጫዎች የተበረከቱ ሲሆን፣ በዘንድሮው ዓመት ደግሞ ድጋፉ በተሻለ ሁኔታ ተጠናክሮ ቀጥሎ ከ5 እስከ 6 ዓመታት የአገልግሎት ዋስትና (ጋራንቲ) ያላቸው 250 ትልልቅ የሶላር መሣሪያዎች ከነባትሪያቸው ለገዳማቱ እንዲደርሱ ተደርጓል።
ይህም በገጠራማ አካባቢዎች ለሚገኙ ገዳማት የመንፈሳዊ አገልግሎት እንቅስቃሴ ትልቅ እፎይታ የሚያበረክት መልካም አጋጣሚ መሆኑ በወቅቱ ተገልጿል።
በሥነ ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የመንበረ ፓትሪያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የገዳማት መምሪያ ኃላፊው መጋቤ ካህናት አባ ሀብተጊዮርጊስ አስራት ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ በተጣበበ የሥራ ሰዓታቸው ተገኝተው ፕሮግራሙን በማካፈላቸው ያላቸውን ደስታ የገለጹ ሲሆን አክለውም የቀረቡት ልዩልዩ ቁሳቁሶች በትክክል ለታለመላቸው መንፈሳዊ ዓላማ እንደሚውሉና የመምሪያው ሐዋርያዊ አገልግሎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።በተጨማሪም ይህ አሠራር መሥሪያ ቤቱን ካልተፈለገ ተጨማሪ ወጪ ያዳነ መሆኑንም ተናግረዋል።
በመጨረሻም ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ ለገዳማትና አድባራት አስፈላጊውን ድጋፍ ላደረጉት ለብፁዕ አቡነ ማርቆስ እና ለገዳማት መምሪያው የላቀ ምስጋና በማቅረብ፣ አባታዊ መመሪያና ቡራኬ ሰጥተው መርሃ ግብሩ በሰላም ተጠናቋል።
ላዕከ ወንጌል ኃይሉ አየለ
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr000080.jpeg 252 448 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-08-30 15:02:522026-08-30 15:02:52የገዳማት መምሪያ ለአህጉረ ስብከትና ገዳማት የሚያገለግሉ ልዩልዩ የቤተ ክርስቲያን መገልገያና የሶላር ኃይል ማመንጫ መሳሪያዎችን አበረከተ።
Search Search

Recent Posts

  • የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት መጪውን በዓል ምክንያት በማድረግ ለቤተ ክርስቲያኗ ከፍተኛ መሪዎች «የእንኳን አደረሳችሁ» ስጦታ አበረከተ።
  • የምስካየ ኅዙናን መድኃኔ ዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰንበት ትምህርት ቤት ላለፉት ሁለት ዓመታት ያሰተማራቸውን ደቀ መዛሙርት አስመረቀ !!!
  • ጳጉሜ የሚለው ስያሜ ‹‹ኤፓጉሜኔ›› ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ ሲሆን ትርጉሙም ‹‹ጭማሪ›› ማለት ነው፡፡ (አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፤ መዝገበ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገብ ቃላት፤ ገጽ ፱፻፭)
  • የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ መምህራንና ሠራተኞች ለተባባሪ ፕሮፌሰር ለብፁዕ አቡነ ፊልጶስ(ዶ/ር) የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በመመረቃቸው ልዩ የደስታና የምስጋና መርሐ ግብር አካሄዱ።
  • “መስከረም በአታ የሃያ ሺህ ሰዎች ምሥረታ” በሚል የታዕካ ነገሥት በአታ ለማርያም ገዳም የአብነት ትምህርት ቤት ሕንጻ ግንባታ ድጋፍ ማስጀመሪያ ጋዜጣዊ መግለጫ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ በተገኙበት ተሰጠ።

Archives

  • September 2026
  • August 2026
  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church
  • Link to Facebook
Link to: “ስለማኅበሩ ስንመሰክር ኑረናል- ይህ መንፈሳዊ ሠራዊትም ሕገ ቤተ ክርስቲያንን የሚያስጠብቅ መሆን አለበት ” ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ Link to: “ስለማኅበሩ ስንመሰክር ኑረናል- ይህ መንፈሳዊ ሠራዊትም ሕገ ቤተ ክርስቲያንን የሚያስጠብቅ መሆን አለበት ” ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ “ስለማኅበሩ ስንመሰክር ኑረናል- ይህ መንፈሳዊ... Link to: ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዕረፍታቸው በዓል መታሰቢያ በሸገር ሀገረ ስብከት በቡራዩ ጉጂ ገፈርሳ መልካ ኖኖ ክፍላተ ከተማ ፊሊ ዶሮ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን ተከበረ። Link to: ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዕረፍታቸው በዓል መታሰቢያ በሸገር ሀገረ ስብከት በቡራዩ ጉጂ ገፈርሳ መልካ ኖኖ ክፍላተ ከተማ ፊሊ ዶሮ ደብረ ፀሐይ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን ተከበረ። ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዕረፍታቸው...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top