የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዘዕስራ ምእት ዐሠርቱ ወስድስቱ ዓመተ ምሕረት

September 11, 2023

ጳጉሜን ፭ ቀን ፳፻ ፲ወ፭ ዓ.ም
*******
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
“””””””””””””””””””””
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !!

👉 በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፤

👉 ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፤

👉 የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ፤

👉በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤
እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤት የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ፡፡

ዘመንን በዘመን እየተካ ፍጥረቱን የሚመግብና የሚመራ እግዚአብሔር አምላካችን እንኳን ከዘመነ ሉቃስ ወደ ዘመነ ዮሐንስ በሰላም አደረሰን አደረሳችሁ !

“ወኀለይኩ መዋዕለ ትካት፤ ተዘከርኩ ዓመተ ዓለም ወአንበብኩ፤ የድሮውን ዘመን አሰብሁ፤ ዓመተ ዓለምን አስታወስሁ፤ አነበብሁም” (መዝ.፸፮ ፥ ፩)፤

አዝማናትና ዓመታት የሚረሱ ሳይሆኑ ሲታወሱ የሚኖሩ እንደሆኑ ቅዱስ ዳዊት በቅዱስ ቅብእ አማካኝነት ባደረበት መንፈስ ቅዱስ ተመርቶ ያስተምረናል፤ እውነት ነው ዓመታት በግድ ያለውድ መታሰባቸው አይቀርም፤ ትዝታቸውም አይጠፋም፤ ትዝታቸውም በመልካም ወይም በመጥፎ ሊሆን እንደሚችል የሚያጠራጥር አይደለም፤
አዝማናትና ዓመታት እንደ ሌላው ፍጥረተ እግዚአብሔር ሁሉ፣ ለፍጥረታት አገልግሎትን ሊሰጡ መልካም ሆነው የተፈጠሩ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ በሰዎች ስሑት ተግባርና አስተሳሰብ ከመልካምነት ወደ ጎጂነት መቀየራቸው የምናስተውለው እውነት ነው፤

አዝማናት ወይም ዓመታት ሰው በሰላም አርሶና ነግዶ ላቡንም አንጠፍጥፎ፣ ጣዕመ ሕይወቱን በአግባቡ ሊመራባቸው ፈጣሪውን ሊያመልክባቸው፣ ሊማርባቸውና ዕውቀት ሊገበይባቸው፣ ሲሳሳትም ንስሐ ገብቶ ሊታረምባቸው የተሰጡ ጸጋዎች ናቸው፤ ሰው አዝማናትን በዚህ ሲጠቀምባቸው መልካም ይሆናሉ በመልካምም ይታወሳሉ፤

ነገር ግን ሰው በቂምና በበቀል፣ በጥላቻና በመናናቅ እንደዚሁም ማቆሚያ በሌለው የራስ ወዳድነት ክፉ መንፈስ ተይዞ እርስ በርስ የሚጋጭባቸው፣ እግዚአብሔርንም ቸል የሚልባቸው፣ ለሥጋዊና ለመንፈሳዊ ሕይወቱ ዘላቂ የጋራ ጥቅም የማይጠቀምባቸው፣ ሁለንተና ሕይወቱን በንስሐ የማይታደስባቸው፣ በፍቅርና በሰላም የማይኖርባቸው ከሆኑ ዓመታቱ መጥፎዎች ይሆኑበታል፣ በመጥፎም ይታወሳሉ፣ ይህ እውነታ በዓለም ታሪክም ሆነ በሀገራችን ታሪክ በተደጋጋሚ መፈጸሙን በውል የምናውቀው ሓቅ ነው፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት !

የሩቅን ዘመን ትተን ባለፉት ጥቂት አዝማናት ያየናቸው ዓመታት በመልካም ትዝታ የሚታሰቡና የሚዘከሩ እንዳልነበሩ ንጹሁ ኅሊናችን ምስክር ነው፡፡ ስሕተቶች እንዴት ተፈጥረውና አድገው ከባድ ችግር ላይ እንደጣሉንም አእምሮአችን አይስተውም፤ እንደባለ አእምሮ፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ አውቀን፣ አክብረንና ጠብቀን ብንመላለስ ኖሮ የሆነውን ክፉ ነገር ሁሉ ማየት አንችልም ነበር፤

ትልቁ የእግዚአብሔር ፈቃድ ከቂም ከበቀል ርቀን ስራችንን በፍቅርና በስምምነት፣ በትዕግሥትና በምክክር እንድንሰራ ነው፤ ከዚህ ወጥተን የቂምና የበቀል ቊርሾ እየመዘዝን እሱንም በመርዛም ኃይለ ቃል እያጀብን በነጐድን ጊዜ ግን ራሳችንን በራሳችን ክፉኛ ከመጉዳታችንም ሌላ የዓለም አጀንዳ ለመሆን ተገደድን፤

ይህን ክፉ ተግባር የፈጸምንባቸው ዓመታት በክፉ እንጂ በመልካም የማይታሰቡ ሆነው አልፈዋል፤ አሁንም ክፉው አስተሳሰባችንና ተግባራችን በአስተማማኝ የተቀረፈ መስሎ አይታይም፤ ከሚገርመው ነገር የችግሩን መንሥኤ ከልብ ሲያጤኑት አሁን እየተፈጸመ ላለው ጥፋት የሚመጥን የችግር ፍሬ ነገር አይገኝበትም፤ ችግር ቢኖርስ እውን በውይይት የማይፈታ ነበርን ? ተብሎ ቢጠየቅም መልስ አይገኝለትም፤

በወሰንና በርእዮተ ዓለም ምክንያት የምናደርገው ክርክርስ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያውያን የሚለውን መርሕ በትክክል ከተገበርን የሚያከራክረው ምኑ ነው? የሀገሪቱ ሕግስ ይህንን መፍታት አይችልም ነበርን ? በወሰን ምክንያት ጠብ የሚነሣውስ መላዋ ኢትዮጵያ የሁሉም ኢትዮጵያውያን መሆንዋን እየረሳን ይሆንን ? በአንድ የበላይ መሪ፣ በአንድ የሀብት ቋት የምንተዳደር የአንድ ኢትዮጵያ ልጆች አይደለንም ወይ?
ኢትዮጵያዊ የሆነ ሁሉ ከዳር እስከዳር ተንቀሳቅሶ እየሰራ እንዳይኖር የከለከለ ሕግና ሥርዓትስ አለወይ ? ካለስ እሱን በምክክር ፈትቶ ስለታላቋ ኢትዮጵያ ብቻ በጋራ መቆም አይበልጥም ወይ? እውነቱ ይህ ከሆነ ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ ተፎካካሪዎች፣ ልኂቃን፣ የስቢክ ማኅበራትና ምሁራን የሆናችሁ፣ የሆነው ሁሉ ትክክል አልነበረምና እባካችሁ ወደ ልባችሁ መለስ በሉና ምርጫችሁን ኢትዮጵያ፣ ሰላምና አንድነት ብቻ አድርጉ፤ ሌላው ሁሉ በዚሁ ስር ነው ያለው፣ በሂደትም ደረጃ በደረጃ እየተስተካከለ ይመጣል፡፡

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት !

ያለፈው ዓመት ያሳረፈብንን ሁለንተናዊ ተጽዕኖ በሚገባ አስተውለን፣ ዳግም ወደ አዲሱ ዓመት እንዳይሸጋገርብን ካላደረግን አዲሱ ዓመት ለኛ የሚሰጠን ትርጉም ምንድን ነው ? ባለፉት ዓመታት በሃይማኖት፣ በባህል በታሪክ፣ በኢኮኖሚ፣ በማኅበራዊና ፖለቲካዊ እንዲሁም በሕዝባችን ሥር የሰደደውን የእርስ በርስ መጠራጠር ከልብ መርምረን ወደ ድሮው እኛነታችን ካልተመለከትንስ አዲስ ዘመን እያልን ማክበራችን ምን ፋይዳ አለው? ይህንን ሁሉ በአዲሱ ዓመት በማጤን ያለፈውን ጎጂ ነገር በመተው፤ ጠቃሚውን ግን ይበልጥ በማጠናከር አዲሱን ዓመት መቀበል አለብን፤

ከሁሉ በላይ ለሀገራችንና ለሕዝባችን የሚጠቅመው ምንድነው? በሚለው በምር መስራት አለብን፤ በመለያየት፣ በመፎካከር፣ በመበቃቀል፣ በመናናቅ፣ የራስን ጥቅም ብቻ ለማስጠበቅ በመጣር፣ ጊዜ አገኘሁ ብሎ ኃይልን በመጠቀም፣ የሕዝብን ጥቅም ማስከበርና የሀገርን አንድነት ማስቀጠል አይቻልም፤ ሀገራችንንና ሕዝባችንን ወደ ዕመቀ ዕመቅ እየከተቱ ያሉ እንደዚህ ያሉ አስተሳሰቦች ናቸው፤ እነዚህ ሁሉ ከአሮጌው ዓመት ጋራ አብረው መወገድ አለባቸው፤

በአዲሱ ዓመት የሰው ሕይወትን የሚቀጥፉ የመሳሪያ አፈ ሙዞች በሙሉ ወደ መጋዝን መግባት አለባቸው፤ ችግሮችን በውይይት፣ አሊያም በሕግ እየተፈቱ የሀገርና የሕዝብ ሉዓላዊነት ነጻነትና አንድነት መረጋገጥ አለበት፤ ሀገርንና ሕዝብን ለዘለቄታው በአንድነት የሚያስቀጥሉ የሕግ የበላይነትን ማክበር፣ እኩልነትን ማረጋገጥ፣ የጋራ ተጠቃሚነትን እውን ማድረግ፣ የተጐዳውን መደገፍ፣ ሆድ የባሰውን ማለዘብ፣ የተጠቃውን ማጽናናት ሲቻል ነው፡፡

በአዲሱ ዓመት ይህንን ለማድረግ በቊርጥ ከተነሣን ሰላማችን ወደነበረበት ይመለሳል፡፡ ሀገራችንም በበረከት ትሞላለች፤ ስለዚህም ኢትዮጵያውያን የሆናችሁ ልጆቻችን ሁሉ ይህንን ጥሪያችንን ተቀብላችሁ የጥፋት መሳሪያችሁንም አስቀምጣችሁ ወደ ሰላም ማእድ ቀርባችሁ በወንድማማችነት መንፈስ ችግራችሁን በክብ ጠረጴዛ በውይይት በመፍታት የሀገሪቱንና የሕዝቡን አንድነት እንድታስቀጥሉ ሁሉን በሚያይ እግዚአብሔር ስም እንማጸናችኋለን፡፡

በመጨረሻም
አዲሱ ዓመት የሰላምና የፍቅር፣ የዕርቅና የይቅርታ የተፈናቀለው ወደቀየው የሚመለስበት፣ ሆድ የባሰው የሚጽናናበት፣ ፍትሕና ርትዕ የሚሰፍንበት የመሳሪያ ድምፅ የማይሰማበት ፍጹም የተግባቦት ዓመት እንዲሆንልን እየጸለይን ሁሉም ኢትዮጵያውያን ልጆቻችን ለዚህ ቅዱስ ጥሪ አዎንታዊ መልስ እንድትሰጡ አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም በድጋሚ እናስተላልፋለን፡፡

እግዚአብሔር አምላክ አዲሱን ዓመት የሰላምና የተግባቦት ዓመት ያድርግልን ፤

እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ
ተክለ ሃይማኖት
መስከረም ፩ ቀን ፳፻ ፲ወ፮ ዓ.ም.
ዋሽንግተን ዲሲ – አሜሪካ

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/2016-cover.jpg 412 400 tc https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg tc2023-09-11 16:45:132023-09-11 16:51:20ቃለ በረከት ዘብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀጳጳስ ዘአኲስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፤ ዘተናገረ በበዓለ ርእሰ ዓውደ ዓመት ዘዕስራ ምእት ዐሠርቱ ወስድስቱ ዓመተ ምሕረት
Search Search

Recent Posts

  • ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ አዲስ የተሠራውን የለገዳዲ አንቀጸ ምሕረት ቅድስት ኪዳነ ምሕረት ሕንጻ ቤተክርስቲያን መረቁ፡፡
  • የወጨ አንቀጸ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አዲሱ ሕንጻ በብፁዕ ጠቅላይ ዋና ሥራ አስኪያጅ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የቦሌ ምዕራፈ ሰማዕታት ወደብረ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል እና ቅድስት አርሴማ ቤተክርስቲያን የተከናወነው የወንዝ ማስቀየስ ሥራ ተጠናቆ በብፁዓን አባቶች ቡራኬ ተመረቀ።
  • በሸገር ሀገረ ስብከት የታነጸው የደብረ ሣህል ቅዱስ ገብርኤል አዲሱ ሕንጻ ቤተክርስቲያን በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ጸሎተ ቡራኬ ተባርኮ ተመረቀ።
  • ብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ የሱማሌ ክልል ጅግጅጋ እና የምስራቅ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በምሥራቅ አርሲ አሰላ ከተማ ደብረ ምጽላል ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ደማቅ አቀባበል ተደረገላቸው

Archives

  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በ ፳፻፲፭ ዓ/ም አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት አካሄዱ። Link to: የመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በ ፳፻፲፭ ዓ/ም አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ዙሪያ ውይይት አካሄዱ። የመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት በ ፳፻፲፭... Link to: በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የ፳፻ ፲ወ፮ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር የዝግጅት ሥራ ግምገማ ተካሔደ ። Link to: በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የ፳፻ ፲ወ፮ዓ.ም የመስቀል ደመራ በዓል አከባበር የዝግጅት ሥራ ግምገማ ተካሔደ ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top