የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ኦርቶዶክሳውያን ብዙኀን መገናኛ ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን

April 13, 2024

ሚያዚያ ፭ ቀን ፳፻፲ወ፮ ዓ.ም
“”””””””””””””””””””””””””
አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ
=============
የኢ.ኦ.ተ.ቤ. ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ “ኦሮቶዶክሳዊያን ብዙኀን መገናኛ ለኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን” በሚል ርዕስ በዛሬው ዕለት የሥልጠና፣ የምክክርና የውይይት መድረክ በጁፒተር ኢንተርናሽናል ሆቴል አካሂዷል።

በመርሐ-ግብሩ ላይ ሦስት መሠረታዊ ጥናታዊ ጽሑፎች ቀርበው በቡድን ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን እነርሱም፦
1ኛ <<ኦርቶዶክሳውያን ማኅበራዊ ሚዲያን
ለሐዋርያዊ አገልግሎት እንዴት እንጠቀም››
በሚል ርእስ በመምህር ዶ/ር አካለወልድ ተሰማ፤
2ኛ ‹‹የሚዲያ ተቋማት ከሕግና ከሥነ–ምግባር
አንጻር በኦርቶዶክሳዊ መነጽር›› በሚል ርእስ በአቶ አያሌው ቢታኒና በዲ/ን ዘካርያስ ወዳጅ፤
3ኛ “የኦርቶዶክሳዊያን እቅበተ እምነት በዘመነ ማኅበራዊ ሚዲያ “በሚል ርእስ በዲ/ን ታደሰ ወርቁ፤ቀርበዋል። የቀረቡትን ጥናታዊ ጽሑፎች መሰረት በማድረግም በየቡድኑ የተነሡት ሀሳቦች በነገው ዕለት በቡድን አወያዮቹ አማካኝነት ቀርበው በሥልጠናው ላይ ጽሑፍ ባቀረቡ ሊቃውንትና ምሁራን መልስና ማብራሪያ የሚሰጥባቸው ከመሆኑም በላይ በብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና በሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ማብራሪያ የሚሰጥባቸው ይሆናል።

በነገው ዕለት “የኦርቶዶክሳውያን የማኅበራዊ ብዙኀን መገናኛ ሙያተኞች የአሠራር ሥነምግባር ምን መምሰል አለበት›› በሚል ርእስ በአቶ ነጻነት ተስፋዬ ጥናታዊ ጽሑፍ ይቀርብና ይህን መሠረት በማድረግ በየ ቡድኑ ውይይት ተደርጎበት የሚቀረበውን ሀሳብ መሠረት በማድረግም የአቋም መግለጫ የሚዘጋጅ ሲሆን የአቋም መግለጫው ሰኞ ጠዋት በጽርሐ መንበረ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በተገኙበት ይነበብና በሥልጠናው ላይ ለተሳተፉ የምስክር ወረቀት ከተሰጠ በኋላ የማስታወሻ ፎቶግራፍ በመነሣት የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ይሆናል።

የኢ.ኦ.ተ.ቤ. ሕዝብ ግንኙነት መምሪያም በሥልጠናው ላይ ከተሳተፉ ኦርቶዶክሳውያን የብዙኀን መገናኛ ባለሙያዎች ጋር በጋራ መሥራት የሚያስችለውን የግንኙነት መስመር በመዘርጋት ወጥ፣ ተዓማኒና ተቋማዊ መረጃዎችን በማቀበል ለአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን እድገት የሚሠራ ይሆናል። በዚህም የመረጃ መዛባት፣ ከተልዕኮና ከመንፈሳዊ እሳቤ ውጪ የሚሰራጩ መልዕክቶችን መበራከት በማስቀረት ተቋማዊ አሠራርን የሚዘረጋ ይሆናል።

በቀጣይ አንድ ወር ውስጥም በየ አህጉረ ስብከቱ የሚገኙ የሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል ኃላፊዎችን ወደ ማዕከል በማስመጣት ተመሳሳይ ስልጠና እንዲሰጣቸው ከተደረገ በኋላ የግንኙነት መስመራችንን በማጠናከር ተቋማዊ የመረጃ ልውውጥን በመፍጠር ወጥና አስተማማኝ ሥርዓትን በመዘርጋት የሕዝብ ግንኙነት ሥራችን ተጨባጭ ውጤት የሚያስመዘግብ እንዲሆን ይደረጋል።

የዛሬው ዕለት የተደረገውንና በነገው ዕለት የሚካሔደውን ሥልጠና፣ ምክክርና ውይይት መነሻ ተደርጎ የሚዘጋጀው የአቋም መግለጫም በመምሪያችን በሚገባ ተደራጅቶ በየመምሪያዎቹ ምላሽ እንዲያገኝ በማድረግ ክፍቶችን የመሙላትና በኦርቶዶክሳውያን የብዙኀን መገናኛ ተቋማትና በመምሪያችን መካከል ተቋማዊ መተማመንን በመፍጠር የወደፊት ሥራዎቻችን የተቃና እንዲሆኑ በማድረግ ለአንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን ተልዕኮ መፋጠን የምንተጋበትን መደላድል እንፈጥራለን።

የኢ.ኦ.ተ.ቤ. ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ፎቶ EOTC TV

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • የድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ያስገኘባው ባለ ሦስት ወለል ሁለገብ ሕንጻ በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ጸሎተ ቡራኬ በዛሬው ዕለት ተመረቋል።
  • የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ሕንጻ ቤተክርስቲያን ዕድሳት ተጠናቆ በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው ተባረከ።
  • በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ ወደ ቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ተጓዘ።
  • አሐዱ ባንክ ላደረገው ሁለተናዊ እገዛ በቋሚ ሲኖዶስ የእውቅናና የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበረከተለት።
  • የመቱ ፈለገ ጥበብ መንፈሳዊ ኮሌጅ የመጀመሪያውን ዙር እጩ መምህራን በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስመረቀ

Archives

  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል  የደምቢ ደሎ ደ/ጸሐይ መድኃኔዓለም ካቴድራልን ቅዳሴ ቤት አከበሩ። Link to: ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል  የደምቢ ደሎ ደ/ጸሐይ መድኃኔዓለም ካቴድራልን ቅዳሴ ቤት አከበሩ። ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል  የደምቢ ደሎ ደ/ጸሐይ መድኃኔዓለም... Link to: ኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ተቋማትና ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሐሰተኛ ወሬ ባለመቀበል እና ባለማስተላለፍ ኃላፊነታቸውን ሊውጡ እንደሚገባ ብፁዕ አቡነ አብርሃም አሳሰቡ። Link to: ኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ተቋማትና ማኅበራዊ ሚዲያዎች ሐሰተኛ ወሬ ባለመቀበል እና ባለማስተላለፍ ኃላፊነታቸውን ሊውጡ እንደሚገባ ብፁዕ አቡነ አብርሃም አሳሰቡ። ኦርቶዶክሳውያን ብዙኃን መገናኛ ተቋማትና ማኅበራዊ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top