ሰኔ ፳፪ ቀን ፳፻ ፲፯ ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን “#ሕገ_ቤተክርስቲያንና_ልማት” በሚል መሪ ቃል በድሬዳዋ ሀገረ ስብከት አድባራትና ገዳማት ለሚገኙ የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤና የልማት ኮሚቴ አመራሮችና አባላት የተዘጋጀ ስልጠና ተካሄደ።

በስልጠናው ላይ የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ክቡር መጋቤ ሠናያት ቀሲስ ኃይለ ማርያም ገብረ ሚካኤል የሀገረ ስብከቱ የየክፍል ኀላፊዎች የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ጸሐፊያን የልማት ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል።

ሕገ_ቤተክርስቲያንና_ልማት በሚል የተዘጋጀውን ስልጠና መጋቤ ሥርዓት ይመር አባተና መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ዘለዓለም ፈቃዱ የሰጡ ሲሆን በስልጠናውም ላይ የተለያዩ ጥያቄዎችና የመወያያ ሐሳቦች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል በመጨረሻም በክቡር ሥራ አስኪያጁ ምላሽ ተሰጥቶባቸው ስልጠናው ተጠናቋል።

©የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ጽሕፈት ቤት