የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

ቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ይዞት የተነሳውን ደንበኛ ተኮር ስርዓት ተፈጻሚ ለማድርግ የመጀመሪያውን ምዕራፍ አጠናቆ በዛሬው እለት በይፋ አስመረቀ

April 23, 2026

ሚያዚያ ፲፭ ቀን ፳፻፲ወ፰ዓ.ም.
ኢኦተቤክ ቤሕአልድ
አዲስአበባ ኢትዮጵያ
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የሸገር ከተማና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም የበላይ ኀላፊ በሚመሩበት በሳልና አባታዊ የአመራር ጥበብ ካደረጉት ሥራና ሠራተኛን የማገናኘት ሥራ አካል የሆነው የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በሚፈለገው ልክ ራሱ እየለወጠ ነው።
ድርጅቱ ጥር 15 ቀን 1990 ዓ.ም አሁን ባለው ተክለቁመና ልክ እንዲመራ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ካስተላፈበት ጊዜ ጀምሮ ደረጃ በደራጃ እየያደገ የመጣና ከ11 በላይ ዋና ሥራ አስኪያጆችን ያፈራረቀ ቢሆንም በ12ኛው የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ በሊቀ ስዩማን እስክንድር ገብረክርስቶስ ድንቅ ጥበብ ቀማሪነት የተጀመረው የለውጥ እንቅስቃሴ በብዙዎች ዘንድ ዓመታትን ይፈጃል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ተአምር በሚባል ደረጃ ለውጥጡን እንዲፋጠን አድርጎታል። በተለይም የወቅቱ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ የሚሰጡት አባታዊ አመራር ክንፍ ያላቸው ሁሉ እንዲበሩ የሚፈቅድ ነፃነትን የሰጠ በመሆኑ ለድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ታላቅ እድል ፈጥሮለታል ።
ድርጅቱ ራሱን በማዘመንና ደንበኛ ንጉሥ ነው የሚለውን ብሂል በማመን ደንበኛ ተኮር ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት ለደንበኞች ምቹ ፣ ማራኪ፣ ጽዱና ውብ ከባቢ በመፍጠር ዘመኑን የዋጀ ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን በመገንዘብ ለተፈጻሚነቱም ሲታትር የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ነው።
የዚህ ድንቅ ሐሳብ ባለቤትና የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ስዩማን እስክንድር ገብረክርስቶስ ከብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አባታዊ መመሪያ በመቀበል ሌሊትና ቀን ያላሰለሰ ጥረት በማድረግና የድርጅቱን የሥራ ኀላፊዎች በማነቃቃት እንዲሁም የድርጅቱ ደንበኞች በየኔነት ሥሜት እንዲሠሩ በማስተባበር ላለፉት ሰባት ወራት ድንቅ አፈጻጸም ማስመዝገባቸውን በቅርቡ መዘገባች የሚታወስ ነው።
በተለያዩ ጊዜያት በዘገባ እናዳሳወቅነው በድርጅቱ በርካት ሥራዎች የተከናወኑ ሲሆን በድርጅቱ የዘመናት ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማያውቅ መልኩ ደንበኛ ተኮር ስርዓትን ለማሳለጥ ሆድና ጀርባ ሆነው ይኖሩ የነበሩ የድርጅቱን ደንበኞች በማግባባትና የእኔ ነው ብለው እንዲያስቡ በማድረግ ከአሥራ አራት ሚሊዮን ብር በላይ የፈጀ የድርጅቱ መገልገያ ቢሮ እድሳት ሠርተዋል።
አዲሱ ቢሮ የድርጅቱን የበላይ ሊቀ ጳጳስ ቢሮን ጨምሮ 16 ዘመናዊ ክፍሎች የሉት ሲሆን ለደንበኞች ምቹ ከመሆኑ ባሻገር ሠራተኞች ደስተኛ ሆነው እንደሠሩ ተደርጎ የታነፀ በመሆኑ ከነባሩ ቢሮ ልዩ ያደርገዋል።
ሥራው ለወራት በልዩልዩ ሁኔታ የቆየ ሲሆን በዛሬው እለትም
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፤
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብጰት ሊቀ ጳጳስ፤
ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽንና የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ሊቀ ጳጳስ፤
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣
ክቡር ሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት የክብር ጠቅላይ ሚንስትር በማኅበራዊ ዘርፍ አማካሪ፣
ክቡር ንቡረዕድ ኤልያስ አብርሃ የጠቅላይ ቤተክህነት የመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
ክቡር ረዳት ፕሮፌሰር ግርማ ባቱ የጠቅላይ ቤተክህነት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ፤
ክቡራን የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያ ኃላፊዎችና የየድርጅቶች ሥራ አስኪያጆች፤
ክቡራን እና ክቡራት የድርጅቱ ሠራተኞች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ስነ-ስርዓት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/0019.jpg 360 640 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-04-23 09:35:402026-05-05 09:39:24ቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ይዞት የተነሳውን ደንበኛ ተኮር ስርዓት ተፈጻሚ ለማድርግ የመጀመሪያውን ምዕራፍ አጠናቆ በዛሬው እለት በይፋ አስመረቀ
Search Search

Recent Posts

  • የርእሰ ገዳማት ወአድባራት ጣና ቅዱስ ቂርቆስ የአራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት ትርጓሜ ምስክር ት/ቤት በባሕር ዳር ከተማ ለሚያስገነባው “የሕክምና መንደር” የመሠረት ድንጋይ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ተቀመጠ።
  • የላሊበላ ቅርሶችን ለመጠበቅ የሚያስችል ውይይት ሊደረግ መሆኑ ተገለጸ።
  • በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የኢንፎርሜሽን ኮሙዩኒኬሽን ቴክኖሎጂ (አይሲቲ) እና የዲጂታል ሽግግር አማካሪ ኮሚቴ ለአስተዳደር ጉባኤው በዲጂታል ቴክኖሎጂ ዘርፍ እየሠራ ያለውን የተለያዩ የጥናት ሰነዶች አቀረበ፡፡
  • የቤቶችና ሕንጻዎች ልማት ድርጅት ሠራተኞቹን አመሰገነ።
  • “ተመራቂዎች በየተሰማሩበት የስምሪት መስክ ሁሉ እንደ መብራት ሊያበሩ ይገባል” ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ

Archives

  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
Link to: የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዕድሳት የደረሰበትን አሁናዊ ሁኔታ በተመለከተ ለቅዱስ ፓትርያርኩ እና ለብፁዓን አባቶች መግለጫ ቀረበ Link to: የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዕድሳት የደረሰበትን አሁናዊ ሁኔታ በተመለከተ ለቅዱስ ፓትርያርኩ እና ለብፁዓን አባቶች መግለጫ ቀረበ የቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ዕድሳት... Link to: ኋላ ቀር የገንዘብ አስተዳደርን በማዘመን የደንበኞችን ውጣ ውረድ የማስቀረት ዓላማን ያነገበው የሞባይል ባንኪንግ አገልግልግሎት በይፋ ተመርቆ ተግባራዊ ተደረገ Link to: ኋላ ቀር የገንዘብ አስተዳደርን በማዘመን የደንበኞችን ውጣ ውረድ የማስቀረት ዓላማን ያነገበው የሞባይል ባንኪንግ አገልግልግሎት በይፋ ተመርቆ ተግባራዊ ተደረገ ኋላ ቀር የገንዘብ አስተዳደርን በማዘመን የደንበኞችን...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top