ቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ይዞት የተነሳውን ደንበኛ ተኮር ስርዓት ተፈጻሚ ለማድርግ የመጀመሪያውን ምዕራፍ አጠናቆ በዛሬው እለት በይፋ አስመረቀ

ሚያዚያ ፲፭ ቀን ፳፻፲ወ፰ዓ.ም.
ኢኦተቤክ ቤሕአልድ
አዲስአበባ ኢትዮጵያ
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽሕፈት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የሸገር ከተማና የደቡብ ምዕራብ ሸዋ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም የበላይ ኀላፊ በሚመሩበት በሳልና አባታዊ የአመራር ጥበብ ካደረጉት ሥራና ሠራተኛን የማገናኘት ሥራ አካል የሆነው የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በሚፈለገው ልክ ራሱ እየለወጠ ነው።
ድርጅቱ ጥር 15 ቀን 1990 ዓ.ም አሁን ባለው ተክለቁመና ልክ እንዲመራ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ካስተላፈበት ጊዜ ጀምሮ ደረጃ በደራጃ እየያደገ የመጣና ከ11 በላይ ዋና ሥራ አስኪያጆችን ያፈራረቀ ቢሆንም በ12ኛው የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ በሊቀ ስዩማን እስክንድር ገብረክርስቶስ ድንቅ ጥበብ ቀማሪነት የተጀመረው የለውጥ እንቅስቃሴ በብዙዎች ዘንድ ዓመታትን ይፈጃል ተብሎ ሲጠበቅ የነበረው ተአምር በሚባል ደረጃ ለውጥጡን እንዲፋጠን አድርጎታል። በተለይም የወቅቱ ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ የሚሰጡት አባታዊ አመራር ክንፍ ያላቸው ሁሉ እንዲበሩ የሚፈቅድ ነፃነትን የሰጠ በመሆኑ ለድርጅቱ ሥራ አስኪያጅ ታላቅ እድል ፈጥሮለታል ።
ድርጅቱ ራሱን በማዘመንና ደንበኛ ንጉሥ ነው የሚለውን ብሂል በማመን ደንበኛ ተኮር ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን በመረዳት ለደንበኞች ምቹ ፣ ማራኪ፣ ጽዱና ውብ ከባቢ በመፍጠር ዘመኑን የዋጀ ስርዓት መዘርጋት አስፈላጊ መሆኑን በመገንዘብ ለተፈጻሚነቱም ሲታትር የቆየ መሆኑ የሚታወቅ ነው።
የዚህ ድንቅ ሐሳብ ባለቤትና የድርጅቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ስዩማን እስክንድር ገብረክርስቶስ ከብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጅ አባታዊ መመሪያ በመቀበል ሌሊትና ቀን ያላሰለሰ ጥረት በማድረግና የድርጅቱን የሥራ ኀላፊዎች በማነቃቃት እንዲሁም የድርጅቱ ደንበኞች በየኔነት ሥሜት እንዲሠሩ በማስተባበር ላለፉት ሰባት ወራት ድንቅ አፈጻጸም ማስመዝገባቸውን በቅርቡ መዘገባች የሚታወስ ነው።
በተለያዩ ጊዜያት በዘገባ እናዳሳወቅነው በድርጅቱ በርካት ሥራዎች የተከናወኑ ሲሆን በድርጅቱ የዘመናት ታሪክ ውስጥ ታይቶ በማያውቅ መልኩ ደንበኛ ተኮር ስርዓትን ለማሳለጥ ሆድና ጀርባ ሆነው ይኖሩ የነበሩ የድርጅቱን ደንበኞች በማግባባትና የእኔ ነው ብለው እንዲያስቡ በማድረግ ከአሥራ አራት ሚሊዮን ብር በላይ የፈጀ የድርጅቱ መገልገያ ቢሮ እድሳት ሠርተዋል።
አዲሱ ቢሮ የድርጅቱን የበላይ ሊቀ ጳጳስ ቢሮን ጨምሮ 16 ዘመናዊ ክፍሎች የሉት ሲሆን ለደንበኞች ምቹ ከመሆኑ ባሻገር ሠራተኞች ደስተኛ ሆነው እንደሠሩ ተደርጎ የታነፀ በመሆኑ ከነባሩ ቢሮ ልዩ ያደርገዋል።
ሥራው ለወራት በልዩልዩ ሁኔታ የቆየ ሲሆን በዛሬው እለትም
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፤
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የራያ ሀገረ ስብጰት ሊቀ ጳጳስ፤
ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽንና የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት ሊቀ ጳጳስ፤
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣
ክቡር ሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት የክብር ጠቅላይ ሚንስትር በማኅበራዊ ዘርፍ አማካሪ፣
ክቡር ንቡረዕድ ኤልያስ አብርሃ የጠቅላይ ቤተክህነት የመንፈሳዊ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
ክቡር ረዳት ፕሮፌሰር ግርማ ባቱ የጠቅላይ ቤተክህነት ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስኪያጅ፤
ክቡራን የጠቅላይ ቤተክህነት የየመምሪያ ኃላፊዎችና የየድርጅቶች ሥራ አስኪያጆች፤
ክቡራን እና ክቡራት የድርጅቱ ሠራተኞች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በታላቅ መንፈሳዊ ስነ-ስርዓት ተመርቆ ለአገልግሎት በቅቷል።