የጌታችን የአምላካችን የመድኃኔዓለም ጥንተ ስቅለት በዓል በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በከታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል በታላቅ ድምቀት ተከበረ፡

መጋቢት 27 ቀን 2018 ዓ.ም
በየዓመቱ መጋቢት 27 ቀን የሚከበረውን የመድኃኔዓለም ጥንተ ስቅለት በዓል በሸገር ከተማ ሀገረ ስብከት በከታ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ካቴድራል በታላቅ ድምቀት የተከበረ ሲሆን በበዓሉ ላይ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ፣ መጋቤ ሐዲስ ለማ በየነ የኦሮምኛ ቋንቋ መገናኛ ብዙኃን ድርጅት (የEOTC AON) ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣መልአከ ሰላም ቀሲስ ዓለማየሁ ተፈራ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ መልአከ ኃይል ቆሞስ አባ አፈወርቅ ዮሐንስ የለሚ ኩራ ፣ የለገ ጣፎ ፣ ለገ ዳዲ ፣ ኩራ ጅዳና ቡራዩ ሶስቱ ክፍለተ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች ፣ የክፍለ ከተማው የልዩ ልዩ የሥራ ኃላፊዎች ፣ የደብሩ ዋና አስተዳደሪ መልአከ አእላፍ ጥዑመ ልሳን ቢሻው ፣የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም እጅግ በርካታ ሕዝበ ክርስቲያን ተገኝተዋል።
የቃል ኪዳኑ ታቦት ዑደት በማድረግ ሕዝበ ክርስቲያኑን ከባረከ በኃላ የካቴድራሉ ሊቃውንት እና የካቴድራሉ ፎኖተ ሰላም ሰንበት ትምህርት ወጣቶች የቅዱስ ያሬድን ዜማ አቅርበዋል፡፡
በመቀጠልም መልአከ ሕይወት ደረጄ ሥዩም የዕለቱን ትምህረተ ወንጌል አስተምረዋል።
በመጨረሻም በብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ እና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ቃለ ምዕዳንና አባታዊ ቡራኬ የሰጡ ሱባኤያችንን ያስፋጸመን አምላካችንን እየመስገንን ሰሙነ ሕማማትን በስግደት ልናስብ ይገባል ብለዋል።በብፁዕነታቸው ቡራኬም የበዓሉ ፍጻሜ ሆነዋል።© EOTC tv