የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ ኢ/ኦ/ተ/ቤ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ርእይ፣ ተልእኮ እና እሴቶች
      • ታሪክ
      • የአደባባይ በዓላት
      • ህግጋት
    • መዋቅር
      • ቅዱስ ሲኖዶስ
      • ሊቃነ ጳጳሳት
      • መምሪያዎች
      • አህጉረ ስብከት
      • ትምህርት ቤቶች
  • አስተምህሮ
    • አእማደ ምሥጢር
      • ምሥጢረ ሥላሴ
      • ምሥጢረ ስጋዌ
      • ምሥጢረ ጥምቀት
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ትንሳኤ ሙታን
    • ምሥጢራተ ቤተክርስትያን
      • ምሥጢር ጥምቀት
      • ምሥጢረ ሜሮን
      • ምሥጢረ ቁርባን
      • ምሥጢረ ንስሐ
      • ምሥጢረ ተክሊል
      • ምሥጢረ ክህነት
      • ምሥጢረ ቀንዲል
    • ልዩ ልዩ
      • ነገረ ድኅነት
      • ነገረ ማርያም
      • ነገረ ቅዱሳን
      • ነገረ መስቀል
      • ተደጋጋሚ ጥያቄዎች እና መልሶቻቸው
  • አገልግሎቶች
    • ሐዋርያዊ ተልእኮ
    • ማኅበራዊ አገልግሎት
    • የልማት እንቅስቃሴዎች
    • ምግባረ ሰናይ
  • መካናት
    • ቅዱሳት መካናት
      • አክሱም ጽዮን
      • ላሊበላ
      • ደብረ ሊባኖስ
      • ማውጫ
    • ቤተ መዛክርት
      • መንበረ ጸባዖት ቅ/ሥላሴ ቤተ መዘክር
      • የዳግማዊ ምኒልክ መታሰቢያ ታዕካ ነገስት በአታ ለማርያም ቤተ መዘክር
      • ማውጫ
    • የጉብኝት መረጃዎች
      • የጉዞ መረጃዎች
      • የሚጠበቅ ሥርዓት
  • ያግኙን
  • English Site
  • Menu Menu

የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡ አስታወቀ።

August 10, 2026
ነሐሴ 4 ቀን 2018 ዓ.ም
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርቱን ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት አቅርቧል።
ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ ያገኘው ጠቅላላ ገቢ ካለፈው 2017 በጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ18,562,565.21 ብር ብልጫ ማሳየቱም ተገልጿል።
ከጠቅላላ ገቢ ውስጥ ከፍተኛውን ድርሻ የያዘው ከድርጅቱ፣ ከመኖሪያ ቤት ኪራይና ከልዩ ልዩ ገቢዎች የተሰበሰበው 226.6 ሚሊዮን ብር ገደማ ሲሆን፣ ከኮሪደር ልማት ጋር ተያይዞ ለፈረሱ ቤቶች ከተከፈለ የካሳ ክፍያ ደግሞ 53.2 ሚሊዮን ብር በላይ፣ ከባንክ ወለድ 6.4 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ድሬዳዋ ከሚገኙ ቤቶች ከ3.5 ሚሊዮን ብር በላይ ተሰብስቧል ተብሏል።
ከዚህ ባሻገር፣ በኮሪደር ልማት ምክንያት የፈረሱ ቤቶችን ካሳ በተመለከተ በ1ኛው እና 2ኛው ዙር በ2017 በጀት ዓመት የተከፈለ 22.1 ሚሊዮን ብር ገደማ የነበረ ሲሆን፣ በ2018 በጀት ዓመት ግን ይህ ክፍያ ወደ 53.2 ሚሊዮን ብር ማደጉ ተጠቅሷል ፣ ከዚህ ውስጥ 7.8 ሚሊዮን ብር ገደማ ገቢ የተደረገ ሲሆን፣ ቀሪውን ገንዘብ ገቢ ለማድረግ ክትትል እየተደረገ ይገኛል ተብሏል።
በተመሳሳይ፣ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽህፈት ቤት ጀርባ የነበሩ መኖሪያ ቤቶች ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በተሰጠ ሙያዊ አስተያየት መሠረት ለተነሱት 22 ግለሰቦችም ድርጅቱ 1.7 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ምትክ መኖሪያ ቤቶችን ሰርቶ ማስረከቡ በሪፖርቱ ቀርቧል።
በተጨማሪም፣ ድርጅቱ በሕግ አገልግሎት በኩል ይከታተላቸው ከነበሩ 10 መዝገቦች ውስጥ 6ቱ ውሳኔ ያገኙ ሲሆን፣ ውል አፍርሰው ለ3ኛ ወገን አሳልፈው የሰጡ ተከራዮች ላይ ሕጋዊ እርምጃ ከመወሰዱ ባሻገር፣ ወርሃዊ ኪራይ ባልከፈሉ አካላት ላይ በተመሠረተ ክስ ከ9 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲከፍሉ በወጡ ውሳኔዎች መሠረት ክትትል እየተደረገ ይገኛል ተብሏል።
ድርጅቱ አሰራሩን ዘመናዊና ግልጽ ለማድረግም የራሱን ድህረ ገጽ (WWW.eotcha.org) እንዲሁም የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮችን ስራ ላይ ያዋለ ሲሆን፣ በተመሳሳይ መልኩ ከዓባይ ባንክ ጋር በመተባበር ተከራዮች ባሉበት ሆነው ክፍያቸውን በቀላሉ እንዲፈጽሙ የሚያስችል የሞባይል ባንክንግና የደወል (Alarm) ሥርዓት ተግባራዊ ማድረጉ ተነግሯል።
በሌላ በኩል ቀደም ሲል የውሃና የኤሌክትሪክ ፍጆታን በተመለከተ በወር ከ15,000 እስከ 20,000 ብር ያወጣ የነበረውን የድርጅቱን ወጪ፣ አሰራሩን በመቀየር ተከራዮች የተጠቀሙበትን ብቻ እንዲከፍሉ በማድረግ ወርሃዊ ወጪውን ወደ 2,000 – 2,500 ብር ዝቅ ማድረግ መቻሉም በሪፖርቱ ቀርቧል።
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሪፖርቱን ተከትሎ ባስተላለፉት አባታዊ መልእክት የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በተገበራቸው አሰራሮች ከነበሩበት ችግሮች እየተላቀቀ መፍትሔም እያገኘ ስለመሆኑን ጠቁመዋል።
ብፁዕነታቸው “ችግሩ ምንድን ነው ፣ ከቤተክርስቲያን ራሳችንን እያስቀደምን ነው ፣ ለመሰባሰባችን ምክንያት የሆነችንን ቤተክርስቲያንን ማስቀደም ይኖርብናል ፣ አካሄዳችን አሠራራችን ሁሉ በጣም የተሻለ መሆን አለበት” ሲሉም አክለዋል።
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ ድርጅቱ በበጀት ዓመቱ ያስመዘገበው ውጤት አበረታች መሆኑንም ገልፀው “አሁንም ከዚህ የተሻለ አሰራራችን ግልፅ እንዲሆን መጠናከር ፣ መበርታት ያስፈልጋል” ብለዋል።
©የኢኦተቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ድርጅት/ EOTC Broadcasting Service Agency/
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on Pinterest
  • Share on LinkedIn
  • Share on Tumblr
  • Share on Vk
  • Share on Reddit
  • Share by Mail
https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/pr000062.jpeg 299 448 eotceth https://eotceth.org/a/wp-content/uploads/eotceth-logo2.svg eotceth2026-08-10 12:44:082026-08-10 12:44:08የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡ አስታወቀ።
Search Search

Recent Posts

  • የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደርና ልማት ድርጅት በበጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም ማስመዝገቡ አስታወቀ።
  • የወልዳ ዱካ ቡኦታና ወልዳ ሥላሴ ጠቅላላ ማኅበራት ከኦሮሚያ ክልል በክረምት ወራት የሚያሠለጥኗቸውን መምህራን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሚሠሩትን ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችንና ሙዚየሙን ጎበኙ፡፡
  • አዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን በተመለከተ በቋሚ ሲኖዶስ ከተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ!
  • “መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ”
  • የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ያስገነባው 1B+G+8 ሕንጻ በቅዱስ ፓትርያርኩ ቡራኬ ተመረቀ።

Archives

  • August 2026
  • July 2026
  • June 2026
  • May 2026
  • April 2026
  • March 2026
  • February 2026
  • January 2026
  • December 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • March 2025
  • February 2025
  • January 2025
  • December 2024
  • November 2024
  • October 2024
  • September 2024
  • August 2024
  • July 2024
  • June 2024
  • May 2024
  • April 2024
  • March 2024
  • February 2024
  • January 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • April 2023
  • March 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • October 2022
© Ethiopian Orthodox Tewahedo Church
  • Link to Facebook
Link to: የወልዳ ዱካ ቡኦታና ወልዳ ሥላሴ ጠቅላላ ማኅበራት ከኦሮሚያ ክልል በክረምት ወራት የሚያሠለጥኗቸውን መምህራን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሚሠሩትን ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችንና ሙዚየሙን ጎበኙ፡፡ Link to: የወልዳ ዱካ ቡኦታና ወልዳ ሥላሴ ጠቅላላ ማኅበራት ከኦሮሚያ ክልል በክረምት ወራት የሚያሠለጥኗቸውን መምህራን በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሚሠሩትን ልዩ ልዩ የልማት ሥራዎችንና ሙዚየሙን ጎበኙ፡፡ የወልዳ ዱካ ቡኦታና ወልዳ ሥላሴ ጠቅላላ ማኅበራት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top